ክርክሩ የአክሲዮን ድርሻ ትርፍ እንዲከፈል የቀረበ ክስን መሰረት ያደረገ ሲሆን ጉዳዩ በተጀመረበት የምእራብ ሐረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ተጠሪ ከሳሽና 1ኛ የከሳሽ ተከሳሽ፣ አመልካች ተከሳሽና የተከሳሽ ከሳሽ እንዲሁም 2ኛ ተጠሪ 2ኛ የተከሳሽ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡
1ኛ ተጠሪ ጥቅምት 23 ቀን 2009 ዓ.ም ፅፎ ባቀረበው ክስ በአመልካች ኩባንያ ውስጥ በልዩ ቁጥር 1457 የተመዘገበ የአክሲዮን ድርሻ ያለኝ ሲሆን በዓመቱ መጨረሻ ሒሳብ ተሰርቶ ሊከፈለኝ ሲገባ ከ2006 እስከ 2008 ያልተከፈለኝ የአክሲዮን ትርፍን ፍርድ ቤቱ ሂሳቡን በማስመርመር በግምት ብር 30,000 እንዲከፈለኝ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡…….