ጉዳዩ የአፈጻጸም ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው፡፡ በሥር ፍርድ ቤት በተደረገው ክርክር የአሁን አመልካች የፍርድ ባለመብት፤ የአሁን ተጠሪ ደግሞ የፍርድ ባለዕዳ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ የአሁን አመልካች በሥር ፍርድ ቤት ያቀረቡት የአፈጻጸም ክስ ይዘት በአጭሩ፡- የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ. 186610 በቀን 25/01/2013 ዓ.ም የስር ፍርድ ቤቶችን ውሳኔ በማሻሻል አመልካች ለተጠሪ ብር 597,662.20 (አምስት መቶ ዘና ሰባት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ሁለት ብር ከሃያ ሳንቲም) እና ወጪ ኪሳራው በዚሁ ልክ እንዲከፍላቸው ወስኗል፤ የስር ከፍተኛ ፍርድ ቤት አመልካች ለተጠሪ በእላፊ የከፈልኩትን ዋና ገንዘብ ብር 397,169.90 (ሶስት መቶ ዘጠና ሰባት ሺህ አንድ መቶ ስልሳ ዘጠኝ ብር ከዘጠና ሳንቲም) በውሳኔው መሰረት የተመለሰልኝ ሲሆን በእላፊ ከከፈልኩት ወጪ እና ኪሳራ ብር 66,369.48 (ስልሳ ስድስት ሺህ ሶስት መቶ ስልሳ ዘጠኝ ብር ከአርባ ስምነት ሳንቲም) ተመላሽ የሚደረግልን ብር 25.511 ሃያ አምስት ሺህ አምስት መቶ አስራ አንድ ብር) ስለሚሆን ይመለስልኝ ሲል ዳኝነት መጠየቁን የሚያሳይ ነው፡፡መልካም ንባብ…………