26
ጉዳዩ የገጠር መሬት ይዞታን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መሀል ሳይንት ወረዳ ፍርድ ቤት ነው፡፡ በሥር ፍ/ቤት በተደረገው ክርክር የአሁን ተጠሪ ከሳሽ፤ የአሁን አመልካች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ ተጠሪ በስር ፍርድ ቤት ባቀረቡት ክስ በመሀለ ሳይንት ወረዳ 01 ቀበሌ ልዩ ቦታው ቀርኖ ሰና በተባለ አካባቢ የሚገኝ እና በምስራቅ የተጓዳ ደሳለኝ፤ በምዕራብ የሙሉ ደሳለው፤ በደቡብ የአብጤ ካሳ፤ በሰሜን የአማረ ገዛኸኝ የሚያዋስኑት እና በይዞታ ማረጋገጫ ማስረጃ የተመዘገበላቸውን መሬት አመልካች አላግባብ የያዘባቸው መሆኑን በመግለጽ መሬቱን እንዲያስረክብቸው ይወሰንላቸው ዘንድ ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ አመልካች በሰጡት መልስ ተጠሪ አለኝ የሚሉት የይዞታ ማረጋገጫ ማስረጃ አላግባብ የወጣ በመሆኑ የቀረበው ክስ ውድቅ ሊደረግ ይገባል በማለት ተከራክረዋል፡፡መልካም ንባብ…
18
የጉዳዩ አመጣጥ ተጠሪ በስር የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት በአመልካች(ስር 1ኛ ተከሳሽ) እና አሁን የሰበር ክርክሩ ላይ በሌሉት አቶ ጀማል ቢዛ(ስር 2ኛ ተከሳሽ) ላይ ባቀረቡት ክስ ከቀደሞ የኪራይ ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ጋር ሀምሌ 1 ቀን 1974ዓ.ም በተደረገ የኪራይ ውል ስምምነት በቀድሞ አጠራር ቀጠና 4 ከፍተኛ 17 ቀበሌ 24 በሆነው የቤ.ቁ 496 የሆነውን ቤት ተከራቼ የምኖር ሲሆን፤ የመንግስት ቤቶች ኤጀንሲ ሲቋቋምም የኪራይ ውል እየተዋዋልኩ የምጠቀምበት ሲሆን ከመንግስት ቤቶች ኤጀንሲ ጋር በ6/10/2004ዓ.ም ስዋዋል የቤቱ ክፍል ብዛት 3 የሰርቪስ ቤት ደግሞ 6 መሆኑ ተገልጾ ተዋውያለሁ፡፡ ከስር 2ኛ ተከሳሽ ጋር ባለኝ የስጋ ዝምድና ምክንያት መኖሪያ ቤት ስለቸገራቸው በአሁኑ ወቅት ቤቱን የለቀቀው ግለሰብ አቶ ገብሬ ወ/ዮሀንስ አንድ አንድ ይዘን እንጠቀም ነበር፡፡ በዚሁ መነሻ ስር 2ኛ ተከሳሽ የይገባኛል ጥያቄ በማንሳት ቤቱን ይዞ አልወጣም በማለት ሁከት የፈጠረብኝ ሲሆን አመልካች ስር 2ኛ ተከሳሽን በ5/5/08ዓ.ም ባስፈረማቸው የኪራይ ውል የቤቱን ክፍሎች ብዛት በመለወጥ አስፈርሟቸዋል፡፡ አመልካች በ17/7/11ዓ.ም በተጻፈ ተጠሪ የራሱ የሆነ ቤት ያለው በመሆኑ በኪራይ ውል እየተገለገሉበት ያለውን ይዞታ ለቀው እንዲወጡ እና እስከ መጋቢት 20 ቀን 2011ዓ.ም ድረስ ለስር 2ኛ ተከሳሽ እንዲያስረክቡ በማለት በጻፈው ደብዳቤ ሁከት የፈጠረብኝ በመሆኑ፤ ስር 2ኛ ተከሳሽም የተጠሪን ቤት አልለቅም በማለት ሁከት ስለፈጠሩብኝ የሁከት ተግባሩ እንዲወገድልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ጥሩ ንባብ…
25
ጉዳዩ የይዞታ ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ነው፡፡ በሥር ፍ/ቤት በተደረገው ክርክር የአሁን አመልካች ከሳሽ፤ የአሁን ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሾች በመሆን ተከራክረዋል፡፡ የአሁን አመልካች በሥር ፍ/ቤት ያቀረቡት ክስ ይዘት በአጭሩ፡- በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 የቤት ቁጥር 441 የሆነውን ቤት ተጠሪዎች የወሰዱባቸው መሆኑን በመግለጽ እንዲመለስላቸው ይወሰንላቸው ዘንድ ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ጥሩ ንባብ…
16
ጉዳዩ ይዞታን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ነው፡፡ በሥር ፍ/ቤት በተደረገው ክርክር የአሁን ተጠሪ ከሳሽ፤ የአሁን አመልካች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ የአሁን ተጠሪ .በሥር ፍ/ቤት ያቀረቡት ክስ ይዘት በአጭሩ፡- በአዲስአበባ ከተማ ቦሌ ክፍለከተማ በተለምዶ እሳት እና ድንገተኛ ግቢ ውስጥ ስፋቱ ከ 75 ካ.ሜ በላይ የሆነ ሰነድ አልባ መኖሪያ ቦታ አለኝ፤ ከ1988 ዓ.ም ጀምሮ በቁጥጥሬ ስር ነበር፤ ይዞታው ለሕዝብ ጥቅም ተፈልጎ በአዋጅ ቁጥር 455/97 ተጠሪን ጨምሮ በአካባቢው የነበርን 16 ሰዎች እንድንለቅ ካሳ እንዲከፈልን ታዟል፤ ካሳ ተከፍሎን ምትክ መሬት እንዲሰጠን ታዞልናል፤ ለተጠሪም በደብዳቤ ተገልጾልኛ፤ በዚሁ መሰረት ወደ ብር 185946 ተከፍሎኛል፤ ምትክ ቦታም ለመረከብ ቅጽ ሞልቻለሁ፤ መሬቱን በቀን 15/5/2009 ዓ.ም ተረክቤ የሊዝ ውል ደግሞ በቀን 22/05/2009 ተዋውለናል፤ ሆኖም ሰነድ እንዲሰጠኝ አመልካችን ስጠይቅ የተሰጠኝ ምላሽ በ1997 ዓ.ም የጋራ መኖሪያ ቤት ስላለሽ ሊሰጥሽ አይገባም ተብያለሁ፤ ሰነዱንም አግዶታል፤ የሰጠኝንም መሬት መልሶ ወስዶታል፤ ተጠሪ መሬቱን እንዳላገኝ የሚከለክል ሕግ የለም፤ ስለሆነም መሬቱን እንዲለቅልኝ፤ የባለቤትነት ማስረጃም እንዲሰጠኝ፤ መሬቱን ለመመለስ አይገደድም ከተባለም ለልማት ተብሎ የተወሰደብኝ መሬት እንዲመለስልኝ ቤት መስሪያ ምትክ ቦታ እንዲሰጠኝ ይወሰንልኝ የሚል ነው፡፡ ጥሩ ንባብ…
16
ጉዳዩ ሁከት እንድወገድ የቀረበ ክርክር ሲሆን ክርክሩን በመጀመሪያ ደረጃ ሥልጣን በተመለከተው የጀረር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተጠሪ በከሳሽነት ፤ አመልካቾች ደግሞ በተከሳሽነት ተከራክረዋል፡፡ ተጠሪ ያቀረቡት ክስ በአጭሩ፡- በልጄ ስም የተመዘገበ ከ30 ዓመት በላይ በይዞታዬ ሥር የሚገኝ መገኛው እና አዋሳኖቹ በክሱ ላይ ከተመለከተው ሁለት መጋዘን ቤቶች ውስጥ አንደኛውን መጋዘን ቤት ለመሸጥ ቀብድ ከተቀበልኩኝ በኋላ አመልካቾች የሁከት ተግባር የፈጠሩብኝ ሲሆን ፤ በሌላ በኩል 8 ሜትር በ 4 ሜትር የሆነ ቦታ ላይ ያረፈ ልጃቸው በውርስ አግኝታ ለሌላ ግለስብ ተሽጦ የነበረውን በማስመለስ በይዞታቸው ሥር በነበረው ቤት ላይ የፈጠሩት ሁከት እንድወገድ ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ጥሩ ንባብ..