የጉዳዩ አመጣጥ ተጠሪ ከአመልካች ጋር የነበራቸው ጋብቻ በ25/4/11ዓ.ም በፍቺ ውሳኔ መፍረሱን ተከትሎ በአመልካች ላይ ባቀረቡት የተሻሻለ የንብረት ክፍፍል ክስ የግል ንብረቴ የሆኑት ከሟች አባቴ ኮሎኔል መከተ አወቀ ያገኘሁት የውርስ ሀብት ብር 723,447.39 ሲሆን ይህንን ገንዘብ ተጠሪ ለአመልካች በአደራ መልክ ብር 465,075.18 በአመልካች ስም በህብረት ባንክ በሂሳብ ቁጥር 14018161601533010 እ.ኤ.አ በ19/7/2015 ገቢ ያደረኩ ሲሆን በተጨማሪም እኤአ በ10/12/2015 በተጠሪ ስም ተመዝግቦ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወጪ አድርጌ ለአመልካች በአደራ መልክ ብር 228,200.00 የሰጠሁ ሲሆን ይህን ገንዘብ በውርስ ያገኘሁት በመሆኑ አመልካች እንዲመልስልኝ፤ የተጠሪ አይነታቸው እና ዋጋቸው የተገለጹ የወርቅ እና የብር ጌጣጌጦች በ24/12/10ዓ.ም አመልካች ስለወሰደብኝ እንዲመልስልኝ እንዲሁም ወጪ፤ ሰነዶች እና እቃዎች(ዝርዝራቸው የተገለጸ) አመልካች እንዲመልስልኝ፤ የንግድ ፈቃድ እንዲዘጋ፡፡በሚል ጠይቀዋል መልካም ንባብ…..