Login
Federal Supreme Court of Ethiopia
Search
  • Home
  • About Us
    • President Message
    • President
      • Current President
      • Former President
    • Vice President
      • Current Vice President
      • Former Vice Presidents
    • History and Traditions
    • Judges
      • Former Judges
    • Vision Mission and Mandate
    • Judicial Administration Council
  • Court Services
    • Registry Services
      • Court Forms and Fees
    • Daily Court Trial Schedule
    • Case Tracker
    • Requesting Court Documents
      • Disposed Cases
    • Court Annexed Mediation
    • Interpretation Services
    • Legal Support
      • Child Justice Project Office
      • Public Defenders Office
  • Going to Court
    • Visiting the Court
      • What Can I see and Do?
    • Courtroom Etiquette
      • Courtroom Rules
    • Criminal: Information for the Accused Person
    • Civil Disputes: Information for Parties
    • Representing Yourself
    • Information for Witness
    • Information for Lawyers
    • FAQ
  • Digital Law Library
    • Annual Reports
    • State of the Judiciary
    • Monthly Judges Seminar
    • Federal Laws
    • Archives
    • Publications
      • Journal
      • Federal Cassation Decision Series
      • Newsletter
    • Judgments
      • Cassation Decisions
      • Supreme Court Decisions
  • News Media
    • Announcements
    • Interactives
      • Photos
      • Video
    • Services for Media
      • Press Releases
      • Press Conference
      • Media Advisories
      • Speeches
  • Contacts
    • Federal Supreme Court
    • Federal High Court
    • Federal First Instance Court
    • Contact and Feedback
  • Tender
  • Judgement Execution Directorate
    • About Judgement Execution Directorate
    • Auction
  • Vacancy
  • Child Justice Project

አቶ አሸናፊ ተስፋዬ እና የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት የሰ/መ/ቁ 259817

Wednesday, June 4, 2025 3094

ጉዳዩ የመንግሰት ሰራተኛ በመስሪያ ቤቱ በተሰጠ ዉሳኔ ላይ ለአስተዳደር ፍርድ ቤት ይግባኝ ማቅረብ የሚችልበት ሁኔታ እና የጊዜ ገደብ የሚመለከት ነዉ፡፡

በኢ.ፌ.ድ.ሪ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አስተዳደር ፍርድ ቤት በነበረው ክርክር አመልካች አመልካች ተጠሪ ተጠሪ ነበሩ፡፡ አመልካች በቀረበባቸው ክስ ከባድ የዲስፕሊን ጥፋት ፈፅመዋል ተብሎ ከሥራ እንዲሰናበቱ ውሳኔ የተሰጠባቸው  እና በዚህ ውሳኔ ቅር ተሰኝተው ለአስተዳደር ፍርድ ቤት ይግባኝ ከማቅረባቸው በፊት የይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜው ያለፈባቸው መሆኑን በመግለፅ ይግባኙ እንዲፈቀድላቸው የይግባኝ ማስፈቀጃ አቅርበው ውድቅ በመደረጉ የቀረበ የሰበር አቤቱታ ነው፡፡መልካም ንባብ…

Read more

አቶ ሳሙኤል ድረስ ደመቀ እና ዳሽን ባንክ አ.ማ የሰ/መ/ቁ 259234

Wednesday, June 4, 2025 3288

ጉዳዩ የስራ ክርክርን የሚመለከት ሆኖ ክርክሩ የተጀመረው በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ነው፡፡በስር ፍርድ ቤት አመልካች ከሳሽ ተጠሪ ደግሞ ተከሳሽ ሆነው ተከራክረዋል፡፡

አመልካች መጋቢት 20 ቀን 2015 ዓ.ም በተጻፈ ክስ በተጠሪ ባንክ ዉስጥ በምክትል ሥራ አስኪያጂነት የስራ መደብ ከሚያዝያ 24 ቀን 2003 ዓ.ም ጀምሮ በራሴ ፍቃድ የስራ ዉሉን እስካቋረጥኩበት ታህሳስ 17 ቀን 2015 ዓ.ም ጠቅላላ ብር 46,191.01(አርባ ስድስት ሺ አንድ መቶ ዘጠና አንድ ከ01/100) እየተከፈለኝ በቋሚነት ተቀጥሬ እሰራ የነበረ ሲሆን ስራዉን በገዛ ፍቃዴ ስለቅ ተጠሪ ሊከፍለኝ የሚገባዉን የተጠራቀመ ፕሮፊደንት ፈንድ፣ የአገልግሎት ክፍያ፣ የተጠራቀመ የአመት ፍቃድ፣ ጠቅላላ ብር 541,422.78(አምስት መቶ አርባ አንድ ሺ አራት መቶ ሃያ ሁለት ከ78/100) ሊከፍለኝ ስላልቻል ይህን ክፍያ እንዲከፍለኝ እንዲሁም ክፍያዉ ለዘገየበት የካሳ ክፍያ፣ ያለስራ ለተቀመጥኩበት የሶስት ወር ደመወዝ ካሳ እና የስራ ልምድ ከእዳ ነፃ ተብሎ እንዲሰጠኝ ይወሰንልኝ በማለት ክስ አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ…    

Read more

አቶ መንገሻ መሮ እና እነ መ/ር መስፍን መንገሻ (2ሰዎች) የሰ/መ/ቁጥር 258429

Wednesday, June 4, 2025 2759

በአመልካቾች የይግባኝ አቤቱታው የቀረበለት የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤትም ተጠሪዎች ከወላጆቻቸው ይዞታ በመውሰድ በራሳቸው ጉልበት እና ገንዘብ ያለሙ እና ለምርትም ሲደርስ ለአመልካች እና ባለቤታቸው እኩል በማካፈል በጋራ ሲጠቀሙ የነበሩ በመሆናቸው እንዲሁም የቤተሰብ አባል በመሆን በቤተሰብ በተመዘገበ ይዞታ ላይ እየተጠቀሙ የነበሩ በመሆናቸው የመጠቀም መብታቸው ቀሪ ሊሆን እና ያፈሩትንም ንብረት ሊያጡ አይገባም፣የስር ፍ/ቤቶችም ተጠሪዎች በይዞታው ላይ መብት የላቸውም በማለት የሰጡት ውሳኔ ተጠሪዎች በይዞታው ላይ ካላቸው መብት እና የቤተሰብ አባልነት አኳያ ለክርክሩ ምክንያት የሆነውም ይዞታው ላይ የሚገኝ ቡና እና ኮረሪማ ባልና ሚስቱ ሊካፈሉ አይገባም፣አመልካች እና ባለቤታቸው ከተጠሪዎች ጋር በጋራ ሊጠቀሙ ይገባል በሚል ወስኗል፡፡ አመልካችም የተሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በሚል ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያቀረቡ ሲሆን አቤቱታው የቀረበለት ችሎትም ውሳኔው የህግ ስህተት አልተፈጸመበትም በማለት ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል፡፡

አመልካችም ለዚህ ሰበር ሰሚ ችሎት ያቀረቡት የሰበር አቤቱታ በአጭሩ ተጠሪዎች በውል ወይንም በውርስ ያገኙት የይዞታ ባለቤትነት መብት ሳይኖራቸው መከራከራቸው በህገ መንግስት አንቀጽ 40/7/8 የተቀመጠውን መብት ጥሰት ነው፡፡ተጠሪዎች መሬቱን ከ2000 ዓ.ም ጀምረው አልምተውታል ቢባል እንኳን አባታቸውን ስላገዙ የባለቤትነት መብት አይሰጣቸውም፡፡የክርክር መነሻ የሆነውን ይዞታ ያገኘሁት በአዋጅ ቁጥር 110/99 መሰረት አርሶአደር በመሆኔ ሲሆን ተጠሪዎች የከተማ ነዋሪዎች እና የመንግስት ሰራተኞች በመሆናቸው በውርስም ከሆነ ከሞትኩ በኃላ የሚፈፀም ይሆናል እንጂ በህይወት እያለው ይዞታውንና ንብረቱን ሊካፈሉ አይችሉም በሚል የተሰጠው ውሳኔ እንዲታረም ጠይቀዋል፡፡  መልካም ንባብ…

Read more

እነ ወ/ሮ ተናኜ ሞላ ብርሐኔ(3ሰዎች) እና አቶ ሳሙኤል ተገኝ ኃይሌ የሰበር መዝገብ ቁጥር - 257774

Wednesday, June 4, 2025 2914

ጉዳዩ የተጀመረው በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሲሆን በስር ፍርድ ቤት አመልካቾች ተጠሪዎች ተጠሪ ደግሞ አመልካች በመሆን ተከራክረዋል፡፡በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካቾች ላይ ያቀረቡት ክስ ይዘት በአጭሩ ወላጅ አባት ሟች አቶ ኃይሌ ተገኝ የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ኑዛዜ የፈፀሙ መሆኑን አመልካች የሟች ብቸኛ ልጅ መሆኑን ለተጠሪዎች ኑዛዜ በመፈፀም ከሚደርሰው ድርሻ ከሩብ በላይ ጉዳት እንዲደርስበት ያደረገ በመሆኑ ከኑዛዜው እንድነቀል ተደርጊያለሁ ስለዚህ ሟች ፈፀመውታል የተባለው ኑዛዜ እንዲሻርልኝ የሚል ነው፡፡

ከአመልካቾች በኩል የተሰጠው መልስ በአጭሩ ኑዛዜው በህግ ፊት የፀና ነው ሟች ማንም ሰው ሳያስገድዳቸው በራሳቸው ፍቃድና ፍላጎት በትክክለኛ አእምሮ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ ፊት ቀርበው የኑዛዜው ሰነድ ተነቦላቸው በምስክሮች ፊት የቁም ኑዛዜ ያደረጉ ስለሆነ ኑዛዜው ህጋዊ መሆኑን ሟች ጥር 29 ቀን 2012 ዓ.ም ባደረጉት የቁም ኑዛዜ በተራ ቁጥር 2፣ 3 እና 4 የተጠቀሱት የኑዛዜ ተቀባዮች በሟች ስም የሚጠሩ መሆናቸውን ኑዛዜ አድራጊው ልጆች ናቸው ብሎ የተቀበላቸውን ግለሰቦች 3ኛ ወገን ተወላጆች ስላልሆኑ የኑዛዜ ስጦታ ሊበረከትላቸው አይገባም ብሎ መከራከር የሟችን በንብረቱ ላይ የማዘዝ መብትን የሚጥስ በመሆኑ ተቀባይነት የሌለው መሆኑን የኑዛዜ ተቀባዮች ተወላጆች አይደሉም ቢባል እንኳን የኑዛዜ ስጦታ ለተወላጅ ብቻ የሚሰጥ መብት ነው የሚል የህግ ድንጋጌ ያለመኖሩን አመልካች ሟች አባታቸው ባደረጉት ኑዛዜ የኑዛዜ ተቀባይ ነው እንጂ በኑዛዜው ከውርስ አልተነቀለም፡፡ አመልካች ከጠየቁት ዳኝነት አንፃር በኑዛዜው የሚደርሳቸውን ድርሻ በትክክል ለይተው አልጠየቁም የሟች ቁም ኑዛዜ ፈራሽ የሚሆንበት በቂ ምክንያት ስላልቀረበ የአመልካች ክስ ውድቅ እንዲደረግ የሚል ነው፡፡መልካም ንባብ…  

Read more

ወ/ሮ ሰላማዊት ያደሳ እነ አቶ ፀሀዬ ጌታቸው(2ሰዎች) የሠ/መ/ቁጥር 256923

Wednesday, June 4, 2025 2809

ጉዳዩ አመልካች ከ1ኛ ተጠሪ ጋር እንደባልና ሚስት አብረዉ በኖሩበት ጊዜ ያፈራነዉ ንብረት ነዉ ያሏቸዉን ንብረቶች ለመካፈል ያቀረቡት ክስ አስቀድሞ ዉሳኔ ባገኘ ጉዳይ ለሁለተኛ ጊዜ የቀረበ ክስ ነዉ በሚል ዉድቅ በመደረገ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል በቀረበ የሰበር አቤቱታ መነሻ የተደረገዉን ክርክር የሚመለከት ነዉ፡፡ ክርክሩ በተጀመረበት በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመልካች በ1ኛ ተጠሪ ላይ በመሰረቱት ክስ የአሁን 2ኛ ተጠሪ ጣልቃ በመግባት የተከራከሩ ሲሆን የክሱ ይዘት በአጭሩ - ከ1ኛ ተጠሪ ጋር ከቀን 15/04/1999 ዓ.ም ጀምሮ እንደባልና ሚስት አብረን ስንኖር ያፈራነው በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ክልል ውስጥ የሚገኝ የቤት ቁጥር 121 የይዞታ መለያ ቁጥር AA000070806106 የሆነና በተጠሪ ስም ተመዝግቦ የሚገኝ ስፋቱ 403 ካሬ ሜትር የሆነ 8 የሚከራዩ ሰርቪስ ቤቶች እና 4 ክፍል ያለው ዋና ቤት እና ቦታ የጋራ ሀብት ስለሆነ ተጠሪ ድርሻዬን እንዲያካፍለኝ በማለት ሌሎች ንብረቶችንም እንደዚሁ በመጥቀስ ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡   መልካም ንባብ…

Read more
FirstPrevious3456789101112NextLast

Categories

  • 2011 Expand/Collapse
  • 2012 Expand/Collapse
  • 2013 Expand/Collapse
    Contacts
  • TEL : +251-11-1-55-34-00 /
  •          +251-11-1-11-04-32
  • Fax : +251 111-550278 /
  •          +251 111-565583
  • Email : fscpublicrelation@gmail.com
  • Address: 6 Killo , Addis Ababa, Ethiopia
Quick Links
  • About Us
  • E-Filing 
  • Calendar
  • Press Release
  • Case Tracker
  • FAQ
    Connect With Us
  • Privacy Policy
  • |
  • Site Map
Copyright © The Federal Supreme Court of Ethiopia- All rights reserved
Powered By Bsquare IT Solutions