ይህ ጉዳይ የተጀመረው በአሶሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች በተጠሪ ላይ ባቀረቡት ክስ በአሶሳ ከተማ የሚገኘውንና እና የይዞታ መለያ ቁጥሩ 72/30/19 የሆነውን ሱቅ ወ/ሮ ትርንጎ በላይ እና አቶ በላይ አበበ ከተባሉ ግለሰቦች ላይ በውል ገዝቼ ውሉ ፀድቆ ስመ-ሀብቱ ወደ እኔ ዞሮ ቁጥሩ 355/164 የሆነ የምስክር ወረቀት ተሰጥቶኝ ለ10 ዓመታት ያክል ስሰራበት ቆይቻለሁ፡፡ ይሁን እንጂ ወ/ሮ ማሪቱ መንጌ የተባለች ግለሰብ በ2008 ዓ.ም በአሶሳ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የይዞታ ይገባኛል ክርክር አቅርባ ጉዳዩን እንዲያጣራ የታዘዘው ተጠሪ ለፍርድ ቤቱ በላከው ማስረጃ አመልካች 15.18 ካ.ሜ ይዞታ እንዳለፍኩኝ ለአሶሳ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመግለጽ በህጋዊ መንገድ ያገኘሁትን ይዞታ በፍርድ አሳጥቶኝ ለከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ የዳረገኝ በመሆኑ ለደረሰብኝ ጉዳት ብር 3,000,000.00 ካሳ እንዲከፍለኝ ይወሰንልኝ በማለት የጠየቀዉን ዳኝነት መነሻ ያደረገ ነዉ፡፡ክሱ እንደሚከተለው ቀርቧል…………….