38
ተጠሪዎች ነሐሴ 03 ቀን 2013 ዓ.ም በተጻፈ አቤቱታ ያቀረቡት ክስ ይዘት፡- ከአመልካች ድርጅት ዉስጥ ለበርካታ ዓመታት በጥበቃ ሠራተኝነት ተቀጥረዉ በማገልገል ላይ እያሉ መንግስት ከሕዳር 04 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በወሰደዉ እርምጃ የአመልካች ድርጅት ከሥራ ታግዶ ይገኛል፡፡ የአመልካች ድርጅት ለዘለቄታዉ በመዘጋቱ ተጠሪዎች ያልተጠቀሙበት የዓመት እረፍት በገንዘብ ተቀይሮ እንዲከፈላቸዉ፤ የሥራ ስንብት ክፍያ፣ ያልተከፈላቸዉ ደመወዝ፣ ክፍያ ለዘገየበት የ 3 ወር ደመወዝ እና የማስጠንቀቂያ ጊዜ ክፍያ እንዲከፈላቸዉ ጠይቀዋል፡፡ ...
54
በስር ፍ/ቤት ተጠሪ በቀን 12/11/2013 ዓ.ም ጽፈው ለፌ/መ/ደ/ቦሌ ምድብ ስራ ክርክር ችሎት ባቀረቡት አቤቱታ፦ በአመልካች ድርጅት ውስጥ ከ12/01/2012 ዓ.ም ጀምሮ በወር 12,200.00 (አስራ ሁለት ሺህ ሁለት መቶ) ብር እየተከፈለኝ በአስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት የስራ መደብ በቋሚነት ተቀጥሬ እስከ 30/08/2013 ዓ.ም ስሰራ ከቆየሁ በኋላ አመልካች በቀን 04/08/2013 ዓ.ም ከተቀጠርኩበት ቀይሮ የመጋዘን ቤት ሰራተኛ እንድሆን ያሳወቀኝ ሲሆን ይህንኑ ተቃውሜ ወደ ተቀጠርኩበት ስራ መደብ እንዲመልሱኝ ብጠይቅም ፈቃደኛ ካለመሆናቸው ባሻገር ሞራሌን የነኩትና ስራውን እንድለቅ ጫና ያደረጉብኝ በመሆኑ ለሚመለከተው የመንግስት አካል አመልክቼ ወደ ስራ መደቤ እንድመለስ ማሳሰቢያ ቢሰጥም እንደውም ተባረሻል በማለት የስራ ውሌን በህገ ወጥ መንገድ ያቋረጡብኝ በመሆኑ በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁ.1156/2011 አንቀጽ 35(1)(ለ) ፣ 40(1 እና 2) ፣43 (4)(ሀ) እና 38 መሰረት የማስጠንቀቂያ ጊዜ ክፍያ ብር 36,000.00 (ሰላሳ ስድስት ሺህ) ፣ የስራ ስንብት ክፍያ ብር16,266.00 (አስራ ስድስት ሺህ ሁለት መቶ ስልሳ ስድስት ብር)፣ ካሳ ብር 73,198.00(ሰባ ሶስት ሺህ አንድ መቶ ዘጠና ስምንት) ፣ያልወሰድት የአመት እረፍት ብር 2,439.00 (ሁለት ሺህ አራት መቶ ሰላሳ ዘጠኝ) ፣ክፍያ በወቅቱ ያልከፈሉኝ በመሆኑ ክፍያ ለዘገየበት ክፍያ ብር 36,600.00 (ሰላሳ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ) በድምሩ ብር 165,105.00( አንድ መቶ ስልሳ አምስት ሺህ አንድ መቶ አምስት ብር) ከጠበቃ አበል 15% ጋር እንዲከፍሉኝ ይወሰንልኝ በማለት ጠይቀዋል፡፡...
37
ለዚህ የሰበር ክርክር መነሻ የሆነው ጉዳይ ሊቀርብ የቻለው አመልካች ነሀሴ 06 ቀን 2014 ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት የሰበር አቤቱታ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰበር ሰሚ ችሎት ግንቦት 12 ቀን 2013 ዓ.ም በመ.ቁ 36032 የአመልካችን የማስፈቀጃ አቤቱታ ውድቅ በማድረግ የሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የህግ አተረጓጎም ስህተት የተፈጸመበት ነው በማለት እንዲታረምላቸው በመጠየቃቸው ነው።
አመልካች በስር ፍርድ ቤት መጋቢት 28 ቀን 2014 ዓም በተፃፈ ባቀረቡት የማስፈቀጃ አቤቱታ የሰበር አቤቱታ ማቅረቢያ ጊዜው ያለፈባቸው በፀና ታመው ሆስፒታል በመቆየታቸውና አሁንም ድረስ ህክምናቸውን እየተከታተሉ መሆኑን፤አንዴ እየተኙ አንዴ እየተነሱ ክስ ቢመስርቱም ጉዳዩን ለመከታተል አለመቻላቸውን በህመሙ ምክንያትም የሰበር አቤቱታውን በተገቢው ጊዜ ማቅረብ አለመቻላቸውን ጠቅሰው የማስፈቀጃ አቤቱታውን ፍርድ ቤቱ እንዲቀበላቸው የጠየቁ ሲሆን አመልካች ያቀረቡት አቤቱታ ከፍርድ ቤቱ መጥሪያ ጋር ለተጠሪ ቢደርሰውም መልሱን ያላቀረበ በመሆኑ መልስ የመስጠት መብቱ ታልፏል፡፡...
18
ጉዳዩ የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይን የሚመለከት ሲሆን ለዚህ ሰበር መነሻ የሆነው አመልካች ሰኔ 13 ቀን 2014 ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት የሰበር አቤቱታ የፌ/ከፍ/ፍ/ቤት በመ.ቁ 277133 በቀን 02/10/2014ዓ.ም የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት በመ.ቁ 125119 በቀን 27/4/2014ዓ.ም የሰጠውን ውሳኔ የሻረበት አግባብ መሰረታዊ የህግ አተረጓጉም ሰህተት የተፈጸመበት ነው በማለታቸው ሲሆን በስር ፍ/ቤት አመልካች ከሳሽ የነበሩ ሲሆን ተጠሪ ደግሞ ተከሳሽ ነበሩ፡፡ ...
17
ጉዳዩ የባል እና ሚስት ንብረት ክፍፍልን የሚመለከት ነው፡፡ ክርክሩ በተጀመረበት በሐዋሳ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የአሁን አመልካች በሚያዝያ 20 ቀን 2013 ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት አቤቱታ ከተጠሪ ጋር በጋብቻ አብረን ስንኖር በሐዋሳ ከተማ መናሐሪያ ክፍለ ከተማ ሚሊኒየም አደባባይ ቀበሌ ውስጥ በተጠሪ ስም ተመዝግቦ የሚገኝ በ325 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ መኖሪያ ቤት፤ በአቶ አክሉሉ ደንቢ ስም የተመዘገበች በተጠሪ ተገዝታ የስም ዝውውር ሳይከናወንባት ተጠሪ በውክልና ይዟት የምትገኝ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 01 ደህ 0051 የሆነች ላዳ ተሽከርካሪ እና የተለያዩ የቤት እቃዎች በጋብቻ እያለን ያፈራን በመሆኑ እንድንከፋፈል ይወሰንልን በማለት ጠይቀዋል፡፡...