9527
ጉዳዩ ከክርክር ጭብጥ አያያዝ ጋር ተያይዞ የቀረበ ሲሆን አቤቱታውም ተፈፅሟልያለትን መሰረታዊ የህግ ስህተት ጠቅሰው በዚህ ችሎት እንዲታረምላቸው ጠይቀዋል፡፡ የቀረበው የሰበር አቤቱታ ተመርምሮ ከለይ በዚህ ፍርድ መግቢያ ሊይ የተመለከተውን ነጥብ ለማጣራት ሲባል ያስቀርባሌልተብሎ ግራ ቀኙ በጽሑፍ እንዲከራከሩ ተዯርጓል፡፡ የጉዳዩ አመጣጥ እና የክርክሩ ይዘት አጠር ባለ መልኩ ከሊይ የተመለከተውን ሲመስል ችሎቱም በሰበር አጣሪው ችሎት ሊጣራ ይገበዋል ተብሎየተያዘውን ነጥብ ለሰበር አቤቱታው መነሻ ከሆነው የስር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ እና ለጉዳዩ አግባብነት ካላቸው ሕጎች ጋር በማገናዘብ መርምሯል፡፡መልካም ንባብ...........
5729
ጉዳዩ የውርስ ንብረት ክርክርን የሚመለከት ነው፡፡አቤቱታውም በክል ፍርድ ቤቶች ውሳኔ ሊይ ተፈፅሟል ያሉትን መሰረታዊ የህግ ስህተት ጠቅሰው በዚህ ችሎት እንዱታረምላቸው ጠይቀዋል፡፡ የቀረበው የሰበር አቤቱታ ተመርምሮ ያስቀርባል በመባለልግራ ቀኙ በፅሁፍ እንዱከራከሩ ተደርጓል፡፡ ችሎቱም የግራ ቀኙን ክርክር ለሰበር አቤቱታው መነሻ ከሆነው የስር ፍርዴ ቤቶች ውሳኔ እና ለጉዲዩ አግባብነት ካሊቸው ሕጎች ጋር በማገናዘብ መርምሯል፡፡ እንግዱህ በኢ.ፌ.ዱ.ሪ. ህገ መንግስትም ሆነ ህገ መንግስቱን መሰረት አድርጎ በወጣው የፌድራል ፍርዴ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 መሰረት ለዚህ ሰበር ሰሚ ችልት የተሰጠው የዳኝነት ሥልጣን መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመባቸውን ማናቸውንም የመጨራሻ ዉሳኔዎችን መርምሮ ማረም ስለመሆኑ የህግ መንግስቱ አንቀጽ 80(3(ሀ)) እና የአዋጁ አንቀፅ 10 ዴንጋጌዎች ያስገነዝባል፡፡ መሠረታዊ የህግ ስህተት ማለት ምን ማለት እንደሆነ በአዋጁ የትርጉም ክፍድ በአንቀጽ 2(4) ስር በዝርዝር ተመልክቷል፡፡ጥሩ ንባብ.......
5700
ጉዳዩ ፍቺን ተከትል የተደረገ የባልና ሚስት የንብረት ክፍፍል ክርክርን የሚመለከት ነዉ፡፡አቤቱታውም በሽማግሌዎች እና በፍርድ ቤት ፊት ቆመዉ የቤቱ የገበያ ዋጋ ብር 1,000,000 እንዯሆነ እራሳቸዉ ገምተዉ ግማሹን ገንዘቡን ከፍለዉ ቤቱን ሇለእራሳቸዉ ለማስቀረት ተጠሪ ተስማምተዋል፤ የሀረሪ ክልል የመጀመሪ ደረጃ እና የክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ይህንኑ የተጠሪን ስምምነት መሠረት በማድረግ በአጣሪ ሽማግላዎች የቀረበዉን የዉሳኔ ሃሳብ ተቀብል ማጽደቁ ተገቢ ሆኖ እያለከ ከቤተሰብ ህጉ ድንጋጌ ውጪ በአዲስ የቀረበዉን የተጠሪን ሀሳብ በመቀበል የሀረሪ ክል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የስር ፍርድ ቤቶችን ዉሳኔ የሻረበት ሁኔታ የህግ አግባብን ያልተከተለ ነው፤ እንዲሁም የጋራ ንብረት ክፍፍልን አስመልክቶ በክልል የቤተሰብ ህግ ማስታወሻ ፡ - ይህ የ ሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነ ድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛ ቤ እ ንጂ ለፍርድ አ ፈጻ ጸም ዓላማ አያገ ለግልም ሊይ የተመሇከተዉን ዴንጋጌ መሠረት ባላደረገ መልኩ ቤቱ በሃራጅ ተሸጦ ይካፈለ መባል መሠረታዊ የህግ ስህተት በመሆኑ ታርሞ ይወሰንልኝ የሚል ነዉ፡፡ጥሩ ንባብ፡፡
12241
መዝገቡ ለሰበር ሰሚ ችሎቱ ሊቀርብ የቻለው ተጠሪ ለአመልካች ቤተሰቦች ለሰጠው ብድር በመያዣነት የያዘውን ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን መሬት መልቀቅ የለበትም በማለት የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር 09429 ነሐሴ 7 ቀን 2013 ዓ/ም በዋለው ችሎት የሰጠውን ውሳኔ የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ሰሚ ችሎቱ በሰበር መዝገብ ቁጥር 09815 ጥር 24 ቀን 2014 ዓ/ም በዋለው ችሎት ማጽናቱ መሰረታዊ የህግ ስህተት ስለሆነ በሰበር ሰሚ ችሎቱ ይታረምልኝ በማለት አመልካች የካቲት 25 ቀን 2014 ዓ/ም በተፃፈ የሰበር አቤቱታ በማመልከታቸው ነው፡፡ጥሩ ንባብ..
6403
ጉዳዩ የገጠር መሬት ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሲናና ወረዳ ፍርድ ቤት ነው፡፡ በሥር ፍርድ ቤት በተደረገው ክርክር የአሁን 1ኛ ተጠሪ ከሳሽ፤ የአሁን 11ኛ እና 12ኛ ተጠሪዎች በቅደም ተከተል 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች፤ የአሁን አመልካች እና ከ2- 10ኛ ተጠሪዎች ደግሞ ጣልቃ ገቦች በመሆን ተከራክረዋል፡፡ የአሁን 1ኛ ተጠሪ በሥር ፍርድ ቤት ያቀረቡት ክስ ይዘት በአጭሩ፡- የአሁን 11ኛ የ12ኛ ተጠሪዎች እና 11ኛ ተጠሪ የ12 ተጠሪ ባለቤት ለ1ኛ ተጠሪ ደግሞ እህት ናቸው፣ አባታችን አቶ ሰፋራ ሆርዶፋ መስከረም 24/2011 ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል፤ አባታችን 8 ልጆች አሉት፤አዋሳኛቸው በክሱ ላይ የተገለጸውን 5 የእርሻ መሬት እና አንድ 20 ዚንጎ ቆርቆሮ መኖሪያ ቤት የአባታችን ንብረት በመሆኑ ተጠሪዎች ድርሻቸውን እንዲያካፈሏቸው ይወሰንላቸው ዘንድ ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ መልካም ንባብ ……