Login
Federal Supreme Court of Ethiopia
Search
  • Home
  • About Us
    • Message from the President
    • History and Traditions
    • Vision Mission and Mandate
    • President
      • Current President
      • Former Presidents
    • Vice President
      • Current Vice President
      • Former Vice Presidents
    • Judges
      • Current
      • Former Judges
    • Judicial Administration Council
    • Court Administration & Directorates
  • Court Services
    • Registry Services
      • Court Forms and Fees
    • Daily Court Trial Schedule
    • Case Tracker
    • Requesting Court Documents
      • Disposed Cases
    • Court Annexed Mediation
    • Interpretation Services
    • Legal Support
      • Child Justice Project Office
      • Public Defenders Office
  • E-Filing
    • Quick Start Guide
      • Registration
      • E-Filing
    • User Guide
    • Rules and Guidelines
    • Forms
    • Tutorials
  • Going to Court
    • Visiting the Court
      • What Can I see and Do?
    • Courtroom Etiquette
      • Courtroom Rules
    • Criminal: Information for the Accused Person
    • Civil Disputes: Information for Parties
    • Representing Yourself
    • Information for Witness
    • Information for Lawyers
    • FAQ
  • Digital Law Library
    • Annual Reports
    • State of the Judiciary
    • Monthly Judges Seminar
    • Federal Laws
    • Archives
    • Publications
      • Journal
      • Federal Cassation Decision Series
      • Newsletter
    • Judgments
      • Cassation Decisions
      • Supreme Court Decisions
  • News Media
    • Announcements
    • Interactives
      • Photos
      • Video
    • Services for Media
      • Press Releases
      • Press Conference
      • Media Advisories
      • Speeches
  • Contacts
    • Federal Supreme Court
    • Federal High Court
    • Federal First Instance Court
    • Contact and Feedback
  • Vacancy

ቻይና ዊ ዩ ኮ (ሊሚትድ) የኢትዮያ ቅርንጫፍ እና አቶ ሞገስ አለሙ የሰ/መ/ቁጥር.221229

Thursday, December 29, 2022 283

ጉዳዩ የጉዳት ካሳ ሃላፊነት የሚመለከት ሲሆን በስር ፍርድ ቤት ከሳሽ ተጠሪ ሲሆን አመልካች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡የክሱ ይዘት ባጭሩ አመልካች ከአሸሬ ዙፋን አንገረብ ፕሮጀክት መንገድ አስፋልት ለመገንባት ከኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን  በዉል የተረከበዉን መንገድ ሲገነባ የተጠሪ ይዞታ የሆነ አንድ ተኩል ሄክታር መሬት ላይ ከግንባታዉ የሚያወጣዉን አላስፈላጊ ቋጥኝ እና አፈር ማስወገጃ በማድረግ መሬቱ ለዘለቀታዉ ሰብል ማምረት እንዳይችል አድርጎብኛል፡፡ከዚህ የእርሻ መሬት በአመት አስር ኩንታል ሰሊጥ ምርት አገኛለሁ፤የአንድ ኩንታል ዋጋ ብር አምስት ሺህ ሲሆን በኣመት ብር ሃምሳ ሺህ ሁኖ የአስር ዓመት ብር አምስት መቶ ሺህ (500,000) ነዉ፡፡ይህንኑ የጉዳት ካሳ እንዲከፍል እንዲሰወን በማለት ዳኝነት የጠየቀ ሲሆን አመልካች በኩል ባቀረበዉ መልስ ይዞታነቱ የተጠሪ የሆነውን ቦታ ለአፈር መድፊያነት ለመጠቀም በ2010ዓ.ም መከራየቱን፤በወቅቱ ለአንድ ዓመት ብር አስር ሺህ መክፈሉን፤በ2011ዓ.ም የኪራይ ዉሉ ባለመታደሱ ተጠሪ በማእካለዊ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክስ አቅርቦ ብር ሰማኒያ ሺህ መክፈሉን እስከ ሚያዝያ 30 2012ዓ.ም ለመጠቀም ተስማመምቶ ጉዳዩ በእርቅ መቋጨቱን እና በተጠቀሰዉ ጊዜ ዉስጥ ስራ ባለመጀመሩ ቦታዉን አለመጠቀሙን እንዲሁም የተጠቀመዉ መሬት ሩቡን ብቻ ስለመሆኑና በዉሉ መሰረት ይህንኑ አስተካከሎ ማስረከብ እንጂ ካሳ የመክፈል ግዴታ የሌለበት መሆኑን ጠቅሶ ክሱ ዉድቅ እንዲደረግ መከራከሩን መዝገቡ ያሣያል፡፡መልካም ንባብ…….

Read more

ነጋቲ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እና አበራሽ በየነ የሰ/መ/ቁጥር 228917

Thursday, December 29, 2022 223

ጉዳዩ የስራ ክርክር ሲሆን ክርክሩ በተጀመረበት በፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን አሠሪ እና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ አመልካች ተከሳሽ ተጠሪዎች ደግሞ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡

ተጠሪዎች በመስከረም 26 ቀን 2014 ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት ክስ ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የስራ መደቦች በተለያየ ጊዜ ተቀጥረን ስንሰራ የቆየን ቢሆንም የሠራተኛ ማህበር መስርታችኋላ እና የምትሰሩት ምርት በገበያ ላይ ተፈላጊ አልሆነም በሚሉ ምክንያቶች በመጋቢት 25 ቀን 2013 ዓ.ም በተጻፈ ማስጠንቀቂያ የአገልግሎት ክፍያ ከፍሎ ከስራ አሰናብቶናል፡፡ አመልካች እኛን ካሰናበተ በኋላ ሌሎች ሠራተኞችን የቀጠረ መሆኑን አረጋግጠናል፡፡ አመልካች ያለበቂ ምክንያት ከህግ ውጪ ከስራ ያሰናበተን በመሆኑ ደመወዝ ከፍሎ ወደስራ እንዲመልሰን ካልሆነም የስንብት እና የካሳ ክፍያ በድምሩ ብር 330,288 እንዲከፈል ይወሰንልን በማለት ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ…….

Read more

ወ/ሮ መሰረት ተሻለ ገ/የስ እና ኮ/ል ኪዳነ ገ/ኪዳን ተወልደመድህን የሰ.መ.ቁ 227876

Thursday, December 29, 2022 278

ጉዳዩ ለሰበር ችሎቱ የቀረበው አመልካች የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በመ.ቁ 167024 በ8/2/14ዓ.ም በሰጠው ውሳኔ እንዲሁም የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት በመ.ቁ 277884 በ30/6/14ዓ.ም በሰጠው ብይን ቅር በመሰኘት በ24/9/14ዓ.ም በተጻፈ የሰበር አቤቱታ ስላቀረቡ ነው፡፡

የጉዳዩ አመጣጥ አመልካች ከተጠሪ ጋር የነበራቸው ጋብቻ በፍቺ ውሳኔ መፍረሱን ተከትሎ በስር የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት በተጠሪ ላይ ባቀረቡት የክስ አቤቱታ በጋብቻ ወቅት በጋራ የተፈሩ ናቸው በማለት በመከላከያ ፋውንዴሽን ለመኮንኖች በጋራ ያስገነባው ባለ 3 መኝታ ቤት ከጋራ ገቢ ብር 128,000.00 ተቆጥቦ ቤቱ ተሰርቶ ያለቀና በቅርብ ርክክብ የሚደረግበት ቤት ያለ በመሆኑ አመልካች ሁለት የጋራ ልጆቻችንን ይዤ ያለሁ ስለሆነ የዚህን ቤት የዋጋውን ግማሽ ለተጠሪ ከፍዬ ቤቱ እንዲሰጠኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ ሌሎች ንብረቶችን ገንዘብን ጨምሮ በመዘርዘር ከተጠሪ ጋር እኩል እንዲካፈሉ እንዲወሰንላቸው ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ የጋራ እዳ ናቸው ያሉትን ገንዘብ በመግለጽ ተጠሪ ግማሹን እንዲከፍሏቸው እንዲሁም ለተጠሪ ልኬያለሁ ያሉትም ገንዘብ እንዲመለስላቸው እንዲወሰንላቸው ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ የልጅ ቀለብንም በተመለከተ ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ…….

Read more

አቶ ታደለ ክፍሌ እና አውፋት ፓስታ እና ማኮሮኒ ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማህበርየሰበር መ/ቁ 227738

Thursday, December 29, 2022 229

ጉዳዩ የአሰሪና ሰራተኛ ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ ወረዳ ፍ/ቤት ሲሆን የአሁኑ አመልካች ከሳሽ በመሆን ተጠሪ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡አመልካች ያቀረቡት ክስ በተጠሪ ፋብሪካ ውስጥ ከ16/04/2011 ዓ.ም ጀምሮ በወር ብር 8156 እየተከፈለኝ በፓስታ ምርት ረዳት ሰራተኛ ሁኜ እየሰራሁ እያለ ያለምንም ጥፋት አንድም ማስጠንቀቂያ ሳይሰጠኝ ያለአግባብ በቀን 05/02/2014 ዓ.ም በተፃፈው ደብዳቤ በህገወጥ ከስራ ያሰናበተኝ በመሆኑ ከህገወጥ የስራ ስንብት ጋር የተያያዙ ክፍያዎች እንዲከፈለኝ እንዲወሰንልኝ በማለት ክስ አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ…….

Read more

ወ/ሮ ያምሮት አያና እና አቶ አዲሱ አያና የሰ.መ.ቁ.227111

Thursday, December 29, 2022 202

የጉዳዩ አመጣጥ ሲታይ ከሳሽ በሥር ፍ/ቤት ባቀረቡት ክስ ተከሳሽ የሟች አባታችን አቶ አያና አስማረ ልጅና ወራሽ መሆኑን በማረጋገጥ የዉርስ ሀብት ድርሻ ይገባኛል በማለት ዳኝነት በመጠየቅ የተወሰነለት ቢሆንም ተከሳሽ ተወለድኩኝ በሚልበት ጊዜ አባታችን በጸና ታሞ ያለና ከሌላ ግለሰብ ጋር ግንኙነት አድረጎ የማያውቅ በመሆኑ የሟች ልጅ ስላልሆነ ተከሳሽ የወሰደዉ የወራሽነት ማስረጃ እንዲሰረዝልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡

ተከሳሽ ባቀረበዉ ክርክር ከሳሽ ከዚህ በፊት ተከሳሽ የሟች ልጅ አይደለም በማለት የወራሽነት ማስረጃ እንዲሰረዝብኝ ዳኝነት ጠይቀዉ ልጅነቴ የጸና በመሆኑ እና በዉርስ ሀብት ክፍፍል ክርክር ላይም ተመሳሳይ ክርክር ቢያነሱም ዉድቅ ተደርጎ ወራሽነቴ የተረጋገጠ በመሆኑ ድጋሚ የቀረበ ክስ ነዉ ፤ከሳሽ የተከሳሽ ካሳሽነት ክስ ሳያቀርቡና ከረጅም ጊዜ ክርክር በኋላ ይህንን ክስ ማቅረባቸዉ አግባብ አይደለም በማለት አቤቱታቸው ውድቅ እንዲደረግልኝ በማለት ተከራክሯል፡፡ ከሳሽ በበኩላቸዉ ባቀረቡት ክርክር ተከሳሽ ያቀረቡት መከራከሪያ ዉድቅ እንዲደረግልኝ በማለት ተከራክሯል፡፡መልካም ንባብ…….

Read more
12345678910NextLast

Categories

  • 2011 Expand/Collapse
  • 2012 Expand/Collapse
  • 2013 Expand/Collapse
    Contacts
  • TEL : +251-11-1-55-34-00 /
  •          +251-11-1-11-04-32
  • Fax : +251 111-550278 /
  •          +251 111-565583
  • Email : fscpublicrelation@gmail.com
  • Address: 6 Killo , Addis Ababa, Ethiopia
Quick Links
  • About Us 
  • E-Filing 
  • Calendar
  • Press Release
  • Case Tracker
  • FAQ
    Connect With Us
  • Privacy Policy
  • |
  • Site Map
Copyright © The Federal Supreme Court of Ethiopia- All rights reserved
Powered By Bsquare IT Solutions