ከክርክሩ መረዳት እንደሚቻለዉ አመልካች ባቀረቡት ክስ በተጠሪ ተቋም ዉስጥ መምህር ስሆን ከተጠሪ ጋር ህዳር 30 ቀን 2009 ዓ/ም በተደረገ የአገልግሎት ስምምነት ዉል ለአራት ዓመት እስከ ህዳር 30 ቀን 2013 ዓ/ም ድረስ ከስራ ግዴታ ዉጪ በመሆን የሶስተኛ ድግሪ ስኮላርሽፕ ፕሮግራም ትምህርቴን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተምሬ ለስምንት ዓመት አገልግሎት ለመስጠት ፤ተጠሪ ደግሞ በየወሩ ደመወዝ እና የተለያዩ ክፍያዎችን ሊከፍለኝ የተስማማን እና ይህ ስምምነት በተለያዩ ምክንያቶች ትምህርቱ የማያልቅ ከሆነ የሚሻሻልበትን አግባብ ለማመቻቸት የተስማማን በመሆኑ በዚህም መሰረት በኮቪድ ወረርሽኝ ምክንያት ትምህርቱን በግዜዉ መጨረስ ስላልቻልኩ ዉሉ እንዲራዘም ጠይቄ ተጠሪ ግንቦት 18 ቀን 2014 ዓ/ም ለሁለት ዓመት ማለትም ከነሐሴ 03 ቀን 2014 ዓ/ም አስከ ነሐሴ 30 ቀን 2016 ዓ/ም ዉሉን ያራዘመ በመሆኑ ነሐሴ 30 ቀን 2015 ዓ/ም የማራዘሚያ ዉል ፈጽመናል ፡፡