Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

ሰባት ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የተሰጠ የህግ ትርጉም

በሐይማኖት ተቋማት ውስጥ አስተዳደራዊ ተግባርን ለማከናወን በተሰማሩ ሰራተኞች የሚነሱ  የስራ ክርክሮችን በተመለከተ ፍርድ ቤቶች የስራ ክርክሩን ተቀብለው አከራክረው ለመወሰን ህጋዊ የዳኝነት ስልጣን ያላቸው ስለመሆኑ ትርጉም ተሰጠ

በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 26 ስር እንደተደነገገው አምስት ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የተሰጠን ትርጉም በተለያዩ ምክንያቶች ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ከሰባት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት እንዲታይ እንደሚደረግ እና በዚህ መልኩ የሚሰጠው የህግ ትርጉም ውሳኔው ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በማናቸውም ደረጃ ለሚገኝ የፌደራል ወይም የክልል ፍርድ ቤት አስገዳጅ እንደሚሆን ተመልክቷል፡፡ 

በዚህ መሰረት ከዚህ ቀደም በሰ/መ/ቁ 234706 “በሲኖዶስ ትዕዛዝ መሰረት እንደ ተጠሪዎች ያሉ አካላት ካልተፈጸሙ ባላቸዉ አሠራር መሰረት በአስተዳደር ረገድ እንዲፈጽሙ ከሚደረግ በቀር ተጠሪዎች በፍርድ ተገደዉ ውዝፍ ክፍያ እንዲፈጽሙ፣ ….. የሚወሰንበት አግባብ የለም፤ የስር ፍርድ ቤቶችም ይህንኑ መሰረት አድርገው በፍ/ብ/ስ/ስህግ ቁጥር 9(1) እና 231(1/ለ) መሰረት መዝገቡን መዝጋት አለባቸው” በማለት የተሰጠው ትርጉም በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 26 መሰረት  በሰበር መዝገብ ቁጥር 265878 ጥቅምት 5 ቀን 2018 ዓ/ም ሰባት ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት ተለውጦ ‹‹በሐይማኖት ተቋማት ውስጥ አስተዳደራዊ ተግባርን ለማከናወን በተሰማሩ ሰራተኞች የሚነሱ የስራ ክርክሮችን በተመለከተ ፍርድ ቤቶች የስራ ክርክሩን ተቀብለው አከራክረው ለመወሰን ህጋዊ የዳኝነት ስልጣን አላቸው›› የሚል ትርጉም ተሰጥቷል፡፡

Previous Article ሰባት (7) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተሰጡ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔዎች ልዩ ዕትም ቁጥር 01
Print
930

Documents to download

  • 265878(.pdf, 745.33 KB) - 72 download(s)

«December 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
24252627282930
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
2930311234

ለፌዴራል ፍርድ ቤቶች ሬጅስትራሮች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

3

ለፌዴራል ፍርድ ቤቶች ሬጅስትራሮች ለሬጅስትራሮች በተዘጋጀ የሥልጠና ሞጁልና ሞጁሉ ከተዘጋጀ በኋላ በወጡ ሕጎች እና በአሰራር የሚታዩ ክፍተቶችንን መሰረት ያደረገ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡

ለህጻናት ተስማሚ የፍትህ ስርአትን በተመለከተ ለተከላካይ...

119

 በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት ከህዳር 27 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት የቆየ ተከታታይ ስልጠና ለተከላካይ ጠበቆች ሰጥቷል፡፡

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች እና የፌደራል የህግና ፍትህ...

177

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች እና የፌደራል የህግና ፍትህ ኢኒስቲትዩት “ትወልድን በስነ-ምግባር ተቋምን በአሰራር ”በሚል መሪቃል 22ኛውን ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስናን ቀን በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በቀን 25/03/2018 ዓ.ም አክብረዋል፡፡

የሀረሪ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ልዑክ ቡድን በፌደራል ጠቅላይ...

167

በሀረሪ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ሰለሀዲን ቶፊቅ የተመራ የልዑክ ቡድን በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በቀን 25/03/2018 ዓ.ም በመገኘት የልምድ ልወውጥ አድርገዋል፡፡

1345678910Last