ሰባት ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የተሰጠ የህግ ትርጉም
በሐይማኖት ተቋማት ውስጥ አስተዳደራዊ ተግባርን ለማከናወን በተሰማሩ ሰራተኞች የሚነሱ የስራ ክርክሮችን በተመለከተ ፍርድ ቤቶች የስራ ክርክሩን ተቀብለው አከራክረው ለመወሰን ህጋዊ የዳኝነት ስልጣን ያላቸው ስለመሆኑ ትርጉም ተሰጠ
በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 26 ስር እንደተደነገገው አምስት ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የተሰጠን ትርጉም በተለያዩ ምክንያቶች ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ከሰባት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት እንዲታይ እንደሚደረግ እና በዚህ መልኩ የሚሰጠው የህግ ትርጉም ውሳኔው ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በማናቸውም ደረጃ ለሚገኝ የፌደራል ወይም የክልል ፍርድ ቤት አስገዳጅ እንደሚሆን ተመልክቷል፡፡
በዚህ መሰረት ከዚህ ቀደም በሰ/መ/ቁ 234706 “በሲኖዶስ ትዕዛዝ መሰረት እንደ ተጠሪዎች ያሉ አካላት ካልተፈጸሙ ባላቸዉ አሠራር መሰረት በአስተዳደር ረገድ እንዲፈጽሙ ከሚደረግ በቀር ተጠሪዎች በፍርድ ተገደዉ ውዝፍ ክፍያ እንዲፈጽሙ፣ ….. የሚወሰንበት አግባብ የለም፤ የስር ፍርድ ቤቶችም ይህንኑ መሰረት አድርገው በፍ/ብ/ስ/ስህግ ቁጥር 9(1) እና 231(1/ለ) መሰረት መዝገቡን መዝጋት አለባቸው” በማለት የተሰጠው ትርጉም በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 26 መሰረት በሰበር መዝገብ ቁጥር 265878 ጥቅምት 5 ቀን 2018 ዓ/ም ሰባት ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት ተለውጦ ‹‹በሐይማኖት ተቋማት ውስጥ አስተዳደራዊ ተግባርን ለማከናወን በተሰማሩ ሰራተኞች የሚነሱ የስራ ክርክሮችን በተመለከተ ፍርድ ቤቶች የስራ ክርክሩን ተቀብለው አከራክረው ለመወሰን ህጋዊ የዳኝነት ስልጣን አላቸው›› የሚል ትርጉም ተሰጥቷል፡፡
930
Documents to download
-
265878(.pdf, 745.33 KB) - 72 download(s)