Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

ብርሃን ባንክ አ/ማ እና ብርሃን ባንክ መሠረታዊ የሠራተኞች ማሕበር የሰ/መ/ቁ. 263727

የሰበር አቤቱታው የቀረበው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሠጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል ነው፡፡ የክርክሩን አመጣጥ ከስር ፍርድ ቤት የመዝገብ ግልባጭ እንደተረዳነው አመልካች የስር ተከሳሽ ሲሆን ተጠሪ ከሳሽ ነበር፡፡ ተጠሪ ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ/ም ጽፎ ባቀረበው ክስ አመልካች ድርጅት ለሁሉም ሰራተኞች በሚል በተጻፈ ጥቅማጥቅም የተወሰነ መሆኑ ተገልጾ እያለ የቤት አበል በተለምዶ በጽሕፈት መደብ ላይ ያልሆኑ /non-clericals/ የሚሰሩ ሰራተኞች አልከፍልም ማለቱ የእኩልነት መብት የሚጥስ በመሆኑ የቤት አበል እንዲከፈል እንዲወሰን ዳኝነት ጠይቋል፡፡ አመልካች በሠጠው መልስ ደብዳቤው ለሁሉም ሠራተኞች በሚል የተጻፈው የተለያየ የጥቅማጥቅም ሁኔታዎች የተካተቱበት ስለሆነ ነው፣ በጽሕፈት መደብ ላይ ላልሆኑ ሰራተኞች የቤት አበል ጥቅማጥቅም አልተወሰነም፣ ጥቅማጥቅም ሳይወሰን ክፍያ እንዲፈጸም ዳኝነት ሊጠየቅበት አይችልም፣ በተመሳሳይ የሥራ መደብ ላይ ለሚሰራ ሠራተኞች የተለያየ ጥቅማጥቅም እንዲያገኙ ያልተወሰነ በመሆኑ የእኩልነት መብትን አልተጣሰም፣ ክሱ ተቀባይነት የለውም በማለት ተከራክሯል፡፡መልካም ንባብ…

Previous Article ተወልደ ግደይ የኤሌክትሪክ ኬብል እና ዋየር ፋብሪካ እናየኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሰ/መ/ቁጥር 262505
Next Article እነ ወ/ሮ ጌጤ ሙለታ(3ሰዎች) እና ወ/ሮ ብርሃኔ ካባ የሰ/መ/ቁ 249367
Print
5262

Documents to download

  • 263727(.pdf, 845.46 KB) - 611 download(s)

«July 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
293012345
6789101112
13141516171819
20212223242526
272829303112
3456789

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ...

181

‎የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ጋር የተቀናጀ አሰራርን በመፍጠር የዳኝነት ስርዓቱን ይበልጥ ለማዘመን የሚያስችል ስምምነት ተፈራርሟል።

ለበጎ ፈቃደኛ ጠበቆችና የህግ አገልግሎት መስጫ ማዕከል...

196

በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ለነጻ የህግ ድጋፍ የሚሰጡ የበጎ ፈቃድ ጠበቆች፣ የስነ ልቦና ባለሙያዎች እና ነፃ የህግ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት አስተባባሪዎች የልምድ ልውውጥና ተግባር ተኮር የዉይይት ተካሂዷል።

በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እየተሰሩ ያሉ የለውጥ...

315

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፕሬዝዳንትነትና ምክትል ፕሬዝዳንትነት ሲያገለግሉ የነበሩ የቀድሞ አመራሮች በፍርድ ቤቱ ተገኝተው አሁን ላይ እየተሰሩ ያሉ ዋና ዋና የለውጥ ስራዎችን በተመለከተ ውይይትና ምልከታ አድርገዋል።

ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል የስራ ማስጀመሪያ...

345

‎በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት የተሰራ ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል (One way mirror) በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አዲስ ከተማ ምድብ ችሎት በይፋ ስራ ጀምሯል።

1345678910Last