Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

ተወልደ ግደይ የኤሌክትሪክ ኬብል እና ዋየር ፋብሪካ እናየኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሰ/መ/ቁጥር 262505

ጉዳዩ ለቅድመ ጥንቃቄ ዕዳን መልሶ የማዋቀር ሥነ ሥርዓትን የሚመለከት ነው፡፡ጉዳዩ የተጀመረው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በአመልካች አቤቱታ አቅራብነት ነው፡፡በአመልካች የቀረበው አቤቱታ ይዘትም በአጭሩ ከተጠሪ ጋር ግንቦት 22 ቀን 2003 ዓ.ም እና ነሀሴ 28 ቀን 2011 በተደረገ የብድር አከፋፈል ስምምነት ብር 692,389,514.50 የብድር ገንዘብ ያለበት መሆኑን፤ብድሩ ተከፍሎ የሚያልቀው የካቲት 27 ቀን 2016 ዓ.ም መሆኑን፤ከዚህ ውሰጥ ብር 419,224,378.70 መክፈሉን፤ ባጋጠመው የውጭ ምንዛሪ እጥረት ምክንያት የፋይናንስ እጥረት ያጋጠመው ቢሆንም አሁን የፋይናንስ እጥረት መሰረት የሆነው የጥሬ እቃ አቅርቦት ችግር በመፈታቱ የፋይናንስ ችግሩ በቅርብ የሚቀረፍ መሆኑን እና ይህም በሚዋቀርለት የዕዳ መክፈያ ጊዜ ውስጥ በተጨባጭ ዕዳውን መክፈል የሚያስችለው መሆኑን እንደዚሁም ሌሎች ምክንያቶችን በመዘርዘር ለቅድመ ጥንቃቄ ዕዳን መልሶ የማዋቀር ሥነ ሥርዓት ተፈቅዶለት ዕዳው ተዋቅሮ የሚከፍልበት ጊዜ እንዲሰጠው፤ዕዳው ሊከፈል የሚችልበትን አማራጭ መፍትሄዎች የሚያጠና ለፍ/ቤቱ፤ለአመልካች እና ለተጠሪ እንዲሁም ሌሎች ገንዘብ ጠያቂዎች ድጋፍ የሚያደርግ እና ሪፖርት የሚያቀርብ ባለሙያ እንዲሾም ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ…

Previous Article አቶ አሸናፊ ተስፋዬ እና የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት የሰ/መ/ቁ 259817
Next Article ብርሃን ባንክ አ/ማ እና ብርሃን ባንክ መሠረታዊ የሠራተኞች ማሕበር የሰ/መ/ቁ. 263727
Print
2949

Documents to download

  • 262505(.pdf, 892.83 KB) - 368 download(s)

«February 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
2627282930311
2345678
9101112131415
16171819202122
2324252627281
2345678

ሥነ-ምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥና የጥቅም ግጭት መከላከልና...

0

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፌዴራል ሥነ-ምግባርና ፀረ -ሙስናና ኮሚሽን ጋር በመተባበር በሥነ-ምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥ እና የጥቅም ግጭት መከላከልና ማስተዳደር ላይ ከፍርድ ቤት ዘርፍ ለተውጣጡ የስራ ሃላፊዎች የካቲት 5 እና 6 ቀን 2018 ዓ.ም ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የኢትዮጵያ...

118

የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት እና የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ቢኒያም ኤሮ ናቸው፡፡

በዳኝነት ስርአቱ ውስጥ ለህጻናት ተስማሚ የፍትህ ስርአትን...

106

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት በዳኝነት ስርአት ውስጥ ለህጻናት ተስማሚ የፍትህ ስርአትን ለማጎልበት ከአጋር ድርጅቶች ጋር የጋራ ውይይት መድረክ በቀን 03/06/2018 ዓ.ም ተካሂዷል።

ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንቶች ...

98

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አዲስ ተሿሚ ምክትል ፕሬዚዳንቶች ክቡር አቶ ልዑል ካህሳይን እና ክቡር አቶ ምትኩ ማዳን በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አመራሮች እና የስራ ሃላፊዎች ጋር በቀን 02/06/2018 ዓ.ም ትውውቅ እና የስራ ጉብኝት አድርገዋል፡፡

በቆይታቸውም የፌደራል ፍርድ ቤቶች የሪፎርም ተግባራት ላይ ገለጻ እና የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶች ላይ ማብራሪያ የቀረበላቸው ሲሆን በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሚገኙ የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶችንም ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

1345678910Last