Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መንገሻ መሮ እና እነ መ/ር መስፍን መንገሻ (2ሰዎች) የሰ/መ/ቁጥር 258429

በአመልካቾች የይግባኝ አቤቱታው የቀረበለት የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤትም ተጠሪዎች ከወላጆቻቸው ይዞታ በመውሰድ በራሳቸው ጉልበት እና ገንዘብ ያለሙ እና ለምርትም ሲደርስ ለአመልካች እና ባለቤታቸው እኩል በማካፈል በጋራ ሲጠቀሙ የነበሩ በመሆናቸው እንዲሁም የቤተሰብ አባል በመሆን በቤተሰብ በተመዘገበ ይዞታ ላይ እየተጠቀሙ የነበሩ በመሆናቸው የመጠቀም መብታቸው ቀሪ ሊሆን እና ያፈሩትንም ንብረት ሊያጡ አይገባም፣የስር ፍ/ቤቶችም ተጠሪዎች በይዞታው ላይ መብት የላቸውም በማለት የሰጡት ውሳኔ ተጠሪዎች በይዞታው ላይ ካላቸው መብት እና የቤተሰብ አባልነት አኳያ ለክርክሩ ምክንያት የሆነውም ይዞታው ላይ የሚገኝ ቡና እና ኮረሪማ ባልና ሚስቱ ሊካፈሉ አይገባም፣አመልካች እና ባለቤታቸው ከተጠሪዎች ጋር በጋራ ሊጠቀሙ ይገባል በሚል ወስኗል፡፡ አመልካችም የተሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በሚል ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያቀረቡ ሲሆን አቤቱታው የቀረበለት ችሎትም ውሳኔው የህግ ስህተት አልተፈጸመበትም በማለት ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል፡፡

አመልካችም ለዚህ ሰበር ሰሚ ችሎት ያቀረቡት የሰበር አቤቱታ በአጭሩ ተጠሪዎች በውል ወይንም በውርስ ያገኙት የይዞታ ባለቤትነት መብት ሳይኖራቸው መከራከራቸው በህገ መንግስት አንቀጽ 40/7/8 የተቀመጠውን መብት ጥሰት ነው፡፡ተጠሪዎች መሬቱን ከ2000 ዓ.ም ጀምረው አልምተውታል ቢባል እንኳን አባታቸውን ስላገዙ የባለቤትነት መብት አይሰጣቸውም፡፡የክርክር መነሻ የሆነውን ይዞታ ያገኘሁት በአዋጅ ቁጥር 110/99 መሰረት አርሶአደር በመሆኔ ሲሆን ተጠሪዎች የከተማ ነዋሪዎች እና የመንግስት ሰራተኞች በመሆናቸው በውርስም ከሆነ ከሞትኩ በኃላ የሚፈፀም ይሆናል እንጂ በህይወት እያለው ይዞታውንና ንብረቱን ሊካፈሉ አይችሉም በሚል የተሰጠው ውሳኔ እንዲታረም ጠይቀዋል፡፡  መልካም ንባብ…

Previous Article እነ ወ/ሮ ተናኜ ሞላ ብርሐኔ(3ሰዎች) እና አቶ ሳሙኤል ተገኝ ኃይሌ የሰበር መዝገብ ቁጥር - 257774
Next Article አቶ ሳሙኤል ድረስ ደመቀ እና ዳሽን ባንክ አ.ማ የሰ/መ/ቁ 259234
Print
2319

Documents to download

  • 258429(.pdf, 1.07 MB) - 311 download(s)

«January 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
2930311234
567891011
12131415161718
19202122232425
2627282930311
2345678

በአገልግሎት አሰጣጥና የተገልጋዩች አያያዝ ላይ ስልጠና ተሰጠ

7

ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰው ሃብት ስራ አመራር ዳይሬክተሮች፣ ቡድን መሪዎች፣ በሬጅስትራር ስር ላሉ እና ለሌሎች የአስተዳደር ዘርፍ ሰራተኞች ጥር 2 ቀን 2018 ዓ.ም በአገልግሎት አሰጣጥና የተገልጋዩች አያያዝ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል ፡፡

በፌዴራል ፍርድ ቤቶች በወንጀል ችሎት በሚታዩ ችግሮችና...

2

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፌዴራል ፍርድ ቤቶች በወንጀል ችሎቶች የሚታዩ ተግዳሮቶችና መፍትሔዎች ዙሪያ በተደረገ የዳሰሳ ጥናት ላይ ጥር 2 ቀን 2018 ዓ.ም የግብዓት ማሰባሰቢያ ዉይይት ተካሄዷል፡፡

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል...

1

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደዉ 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ስብሰባ በህገ-መንግስቱ አንቀጽ 81(2) መሰረት 34 የከፍተኛ ፍርድ ቤት እጩ ዳኞችን ሹመት አጽድቋል፡፡

የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞች በፌደራል...

1

የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞች በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ከቀን 21/04/2018 ዓ.ም እስከ 27/04/2018 ዓ.ም ለተከታታይ 5 የስራ ቀናት ጉብኝት እና ውይይት አድርገዋል፡፡

1345678910Last