ኤልያስ ዳሪ እና እነ ወ/ሮ ሰናይት አብርሃ (6) ሰዎች የሰ/መ/ቁ. 253783
ጉዳዩ የሽያጭ ውል ይፈጸምልኝ ክስ ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ በተጀመረበት በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አመልካች ባቀረቡት ክስ 1ኛ ተጠሪ ሚስትና የወራሽ ወኪል ሆነው ከ3ኛ-6ኛ ያሉት ተጠሪዎች ጋር በጋራ በመሆን በድሮ ቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 3 የይዞታ መለያ ቁጥር AA000040301555 የሆነ በ348 ካ.ሜ ላይ ያለውን ቤትና ይዞታቸውን ጥቅምት 24 ቀን 2011 ዓ/ም በተደረገ የሽያጭ ውል በብር 2,900,000 ሸጠውልኝ በዚህ ውል መሰረት ለሻጮች በየድርሻቸው መጠን እንዲካፈሉት በቼክ ለሁሉም ግማሽ ክፍያው የተከፈላቸው ሲሆን በሽያጭ ውሉ መሰረት ውሉ በተደረገ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የሽያጭ ውሉ ፎርማሊቲውን አሟልተው ውሉን በሰነዶች ምዝገባ ጽ/ቤት ቀርበው ሲያስመዘግቡና ቤትና ይዞታውን ከቤቱ አስረጂ ሰነድ ጋር ሲያስረክቡኝ ቀሪውን ገንዘብ ልከፍላቸው የተስማማን ሲሆን ተጠሪዎች በውሉ መሰረት እንዲፈጽሙ በተደጋጋሚ ብጠይቅም 1ኛ እና 2ኛ ተጠሪዎች ፍቃደኛ ሲሆኑ ከ3ኛ እስከ 6ኛ ያሉ ተጠሪዎች ግን ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ተጠሪዎች በውሉ የተጠቀሰውን ቤት ከነይዞታው ቤቱን ከሚመለከቱ ሰነዶች ጭምር እንዲያስረክቡኝ እንዲወሰንልኝ፤ እንዲሁም የቤቱን ስመሀብት ከሻጮች ወደ ገዢ ለማስተላለፍ የሚያስፈልጉ ፎርማሊቲዎችን እንዲያሟሉ ይወሰንላቸው ዘንድ ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ….
2646
Documents to download
-
253783(.pdf, 848.53 KB) - 380 download(s)