Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

ኤልያስ ዳሪ እና እነ ወ/ሮ ሰናይት አብርሃ (6) ሰዎች የሰ/መ/ቁ. 253783

ጉዳዩ የሽያጭ ውል ይፈጸምልኝ ክስ ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ በተጀመረበት በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አመልካች ባቀረቡት ክስ 1ኛ ተጠሪ ሚስትና የወራሽ ወኪል ሆነው ከ3ኛ-6ኛ ያሉት ተጠሪዎች ጋር በጋራ በመሆን በድሮ ቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 3 የይዞታ መለያ ቁጥር AA000040301555 የሆነ በ348 ካ.ሜ ላይ ያለውን ቤትና ይዞታቸውን ጥቅምት 24 ቀን 2011 ዓ/ም በተደረገ የሽያጭ ውል በብር 2,900,000 ሸጠውልኝ በዚህ ውል መሰረት ለሻጮች በየድርሻቸው መጠን እንዲካፈሉት በቼክ ለሁሉም ግማሽ ክፍያው የተከፈላቸው ሲሆን በሽያጭ ውሉ መሰረት ውሉ በተደረገ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የሽያጭ ውሉ ፎርማሊቲውን አሟልተው ውሉን በሰነዶች ምዝገባ ጽ/ቤት ቀርበው ሲያስመዘግቡና ቤትና ይዞታውን ከቤቱ አስረጂ ሰነድ ጋር ሲያስረክቡኝ ቀሪውን ገንዘብ ልከፍላቸው የተስማማን ሲሆን ተጠሪዎች በውሉ መሰረት እንዲፈጽሙ በተደጋጋሚ ብጠይቅም 1ኛ እና 2ኛ ተጠሪዎች ፍቃደኛ ሲሆኑ ከ3ኛ እስከ 6ኛ ያሉ ተጠሪዎች ግን ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ተጠሪዎች በውሉ የተጠቀሰውን ቤት ከነይዞታው ቤቱን ከሚመለከቱ ሰነዶች ጭምር እንዲያስረክቡኝ እንዲወሰንልኝ፤ እንዲሁም የቤቱን ስመሀብት ከሻጮች ወደ ገዢ ለማስተላለፍ የሚያስፈልጉ ፎርማሊቲዎችን እንዲያሟሉ ይወሰንላቸው ዘንድ ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ….  

Previous Article የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አቶ መጣልኝ መላኩ የሰ.መ.ቁ.252953
Next Article የኢትዮጵያ መድን ድርጅት እና አቶ አበራ ተፈሪ የሰ/መ/ቁጥር 254101
Print
2646

Documents to download

  • 253783(.pdf, 848.53 KB) - 380 download(s)

«January 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
2930311234
567891011
12131415161718
19202122232425
2627282930311
2345678

በአገልግሎት አሰጣጥና የተገልጋዩች አያያዝ ላይ ስልጠና ተሰጠ

7

ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰው ሃብት ስራ አመራር ዳይሬክተሮች፣ ቡድን መሪዎች፣ በሬጅስትራር ስር ላሉ እና ለሌሎች የአስተዳደር ዘርፍ ሰራተኞች ጥር 2 ቀን 2018 ዓ.ም በአገልግሎት አሰጣጥና የተገልጋዩች አያያዝ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል ፡፡

በፌዴራል ፍርድ ቤቶች በወንጀል ችሎት በሚታዩ ችግሮችና...

2

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፌዴራል ፍርድ ቤቶች በወንጀል ችሎቶች የሚታዩ ተግዳሮቶችና መፍትሔዎች ዙሪያ በተደረገ የዳሰሳ ጥናት ላይ ጥር 2 ቀን 2018 ዓ.ም የግብዓት ማሰባሰቢያ ዉይይት ተካሄዷል፡፡

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል...

1

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደዉ 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ስብሰባ በህገ-መንግስቱ አንቀጽ 81(2) መሰረት 34 የከፍተኛ ፍርድ ቤት እጩ ዳኞችን ሹመት አጽድቋል፡፡

የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞች በፌደራል...

1

የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞች በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ከቀን 21/04/2018 ዓ.ም እስከ 27/04/2018 ዓ.ም ለተከታታይ 5 የስራ ቀናት ጉብኝት እና ውይይት አድርገዋል፡፡

1345678910Last