Selam Warga / Wednesday, June 4, 2025 / Categories: CASSATION, Cassation እስጢፋኖስ /ዩቡና/ ዲራጎ እና የሲዳማ ክልል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የሠ/መ/ቁጥር 251519 አመልካች በቀን 26/11/2015ዓ/ም የተጻፈ የሰበር አቤቱታ የቀረበውም የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሰጠው የጥፋተኝነት እና የቅጣት ውሳኔ በክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት መጽናቱ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ነው በማለት ሲሆን ይዘቱ በአጭሩ - አመልካች ድርጊቱ በተፈጸመበት ቦታ ነበርኩኝ እንጂ ድርጊቱን አልፈጸምኩም፤ የተጠሪ ምስክሮች ድርጊቱን ስለመፈጸሜ አላስረዱብኝም፤ ባቀረብኩት ምስክር ወንጀሉን ያልፈጸምኩ መሆኑን አስረድቻለሁ፤የተጠሪ ምስክሮች እርሱን ይመስላል ከማለት ውጪ ድርጊቱን ስለመፈጸሜ አላስረዱም፡፡የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የስር ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሰጠዉን ዉሳኔ በማጽናት የወሰነዉ በወንጀል ሕግ አንቀጽ 23/2 ስር በተደነገገዉ መሠረት የግድያ ወንጀል መፈጸሜ ሳይረጋገጥ በመሆኑ ዉሳኔዉ ከዚህ ድንጋጌ አፈጻጸም ጋር በተያያዘ በሰ/መ/ቁጥር 22069 ስር የተሰጠዉን አስገዳጅ የሕግ ትርጉም የሚቃረን ነዉ፡፡ስለሆነም ተጠሪ ያቀረባቸው ምስክሮች አመልካች ድርጊቱን ስለመፈጸሜ ከጥርጣሬ በላይ ያላስረዱ ስለሆነ የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠው የጥፋተኝነት እና የቅጣት ውሳኔ ተሽሮ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የሰጠው ውሳኔ እንዲጸናል፡፡የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠዉ የጥፋተኝነት ውሳኔው የሚያጸና ከሆነም አንቀጹ ወደ ወንጀል ሕግ አንቀጽ 540 እንዲቀየርልኝ እና የ3ኛ አመት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ስለሆንኩ ቅጣቱ በወ/ህ/አንቀጽ 192 መሰረት እንዲገደብልኝ በማለት አመልክቷል፡፡መልካም ንባብ…. Previous Article የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ቀበሌ 11/12/08 ሸማቾች ኃ/የተ/ሕ/ሥ/ማ እና አቶ እንኮሳ አመንቴ ሱፋ(9ሰዎች)የሰ.መ.ቁ 249104 Next Article ጠቋሬ ፈለቀ እና አባ ምትኩ ዘዉዴ የሰ.መ.ቁ.253916 Print 2881 Documents to download 251519(.pdf, 865.01 KB) - 354 download(s)
አዲስ ለተቀጠሩ ህግ ጉዳይ ጸሐፊ I እና የህግ ጉዳይ... አዲስ ለተቀጠሩ ህግ ጉዳይ ጸሐፊ I እና የህግ ጉዳይ... Tuesday, February 17, 2026 1 አዲስ ለተቀጠሩ ህግ ጉዳይ ጸሐፊ I እና የህግ ጉዳይ ጸሐፊ II በ ቀን 06 እና 09/06/2018 ዓ.ም የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አጠቃላይ ነባራዊ ሁኔታን እና ከለዉጥ ስራዎች ጋር ለማስተዋወቅ የመግቢያ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ Read more
ሥነ-ምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥና የጥቅም ግጭት መከላከልና... ሥነ-ምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥና የጥቅም ግጭት መከላከልና... Monday, February 16, 2026 6 የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፌዴራል ሥነ-ምግባርና ፀረ -ሙስናና ኮሚሽን ጋር በመተባበር በሥነ-ምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥ እና የጥቅም ግጭት መከላከልና ማስተዳደር ላይ ከፍርድ ቤት ዘርፍ ለተውጣጡ የስራ ሃላፊዎች የካቲት 5 እና 6 ቀን 2018 ዓ.ም ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ Read more
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የኢትዮጵያ... የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የኢትዮጵያ... Friday, February 13, 2026 138 የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት እና የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ቢኒያም ኤሮ ናቸው፡፡ Read more
በዳኝነት ስርአቱ ውስጥ ለህጻናት ተስማሚ የፍትህ ስርአትን... በዳኝነት ስርአቱ ውስጥ ለህጻናት ተስማሚ የፍትህ ስርአትን... Wednesday, February 11, 2026 110 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት በዳኝነት ስርአት ውስጥ ለህጻናት ተስማሚ የፍትህ ስርአትን ለማጎልበት ከአጋር ድርጅቶች ጋር የጋራ ውይይት መድረክ በቀን 03/06/2018 ዓ.ም ተካሂዷል። Read more
12Dec2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ የሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Friday, December 12, 2025 Read more
6Nov2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ ሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Thursday, November 6, 2025 Read more
8Oct2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ ሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Wednesday, October 8, 2025 Read more