Selam Warga / Wednesday, June 4, 2025 / Categories: CASSATION, Cassation እስጢፋኖስ /ዩቡና/ ዲራጎ እና የሲዳማ ክልል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የሠ/መ/ቁጥር 251519 አመልካች በቀን 26/11/2015ዓ/ም የተጻፈ የሰበር አቤቱታ የቀረበውም የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሰጠው የጥፋተኝነት እና የቅጣት ውሳኔ በክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት መጽናቱ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ነው በማለት ሲሆን ይዘቱ በአጭሩ - አመልካች ድርጊቱ በተፈጸመበት ቦታ ነበርኩኝ እንጂ ድርጊቱን አልፈጸምኩም፤ የተጠሪ ምስክሮች ድርጊቱን ስለመፈጸሜ አላስረዱብኝም፤ ባቀረብኩት ምስክር ወንጀሉን ያልፈጸምኩ መሆኑን አስረድቻለሁ፤የተጠሪ ምስክሮች እርሱን ይመስላል ከማለት ውጪ ድርጊቱን ስለመፈጸሜ አላስረዱም፡፡የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የስር ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሰጠዉን ዉሳኔ በማጽናት የወሰነዉ በወንጀል ሕግ አንቀጽ 23/2 ስር በተደነገገዉ መሠረት የግድያ ወንጀል መፈጸሜ ሳይረጋገጥ በመሆኑ ዉሳኔዉ ከዚህ ድንጋጌ አፈጻጸም ጋር በተያያዘ በሰ/መ/ቁጥር 22069 ስር የተሰጠዉን አስገዳጅ የሕግ ትርጉም የሚቃረን ነዉ፡፡ስለሆነም ተጠሪ ያቀረባቸው ምስክሮች አመልካች ድርጊቱን ስለመፈጸሜ ከጥርጣሬ በላይ ያላስረዱ ስለሆነ የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠው የጥፋተኝነት እና የቅጣት ውሳኔ ተሽሮ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የሰጠው ውሳኔ እንዲጸናል፡፡የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠዉ የጥፋተኝነት ውሳኔው የሚያጸና ከሆነም አንቀጹ ወደ ወንጀል ሕግ አንቀጽ 540 እንዲቀየርልኝ እና የ3ኛ አመት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ስለሆንኩ ቅጣቱ በወ/ህ/አንቀጽ 192 መሰረት እንዲገደብልኝ በማለት አመልክቷል፡፡መልካም ንባብ…. Previous Article የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ቀበሌ 11/12/08 ሸማቾች ኃ/የተ/ሕ/ሥ/ማ እና አቶ እንኮሳ አመንቴ ሱፋ(9ሰዎች)የሰ.መ.ቁ 249104 Next Article ጠቋሬ ፈለቀ እና አባ ምትኩ ዘዉዴ የሰ.መ.ቁ.253916 Print 4248 Documents to download 251519(.pdf, 865.01 KB) - 514 download(s)
በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እየተሰሩ ያሉ የለውጥ... በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እየተሰሩ ያሉ የለውጥ... Monday, June 8, 2026 5 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፕሬዝዳንትነትና ምክትል ፕሬዝዳንትነት ሲያገለግሉ የነበሩ የቀድሞ አመራሮች በፍርድ ቤቱ ተገኝተው አሁን ላይ እየተሰሩ ያሉ ዋና ዋና የለውጥ ስራዎችን በተመለከተ ውይይትና ምልከታ አድርገዋል። Read more
ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል የስራ ማስጀመሪያ... ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል የስራ ማስጀመሪያ... Thursday, May 28, 2026 38 በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት የተሰራ ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል (One way mirror) በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አዲስ ከተማ ምድብ ችሎት በይፋ ስራ ጀምሯል። Read more
ለሶሻል ወርክ ባለሞያዎች በተዘጋጀ የስልጠና ማንዋል ረቂቅ... ለሶሻል ወርክ ባለሞያዎች በተዘጋጀ የስልጠና ማንዋል ረቂቅ... Monday, May 25, 2026 61 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህፃናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት በፍትህ ስርዓት ውስጥ የሚያገለግሉ የማህበራዊ ሳይንስ ባለሞያዎችን ሚና ለማጎልበት የሚያግዝ የስልጠና ማንዋል የመጨረሻ ረቂቅ ሰነድ ላይ የውይይት እና የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ተካሂዷል፡፡ Read more
የኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፍተኛ ልዑካን ቡድን... የኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፍተኛ ልዑካን ቡድን... Thursday, May 21, 2026 74 በኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ እና የጄሲኢ (JCE) ሰብሳቢ በሆኑት በክብርት ዳኛ ሱዛን ኞኪ ንዱንጉ የተመራው ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ላለፉት ሦስት ተከታታይ ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር አጠናቋል። Read more
10Mar2026 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ የሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Tuesday, March 10, 2026 Read more