Selam Warga / Wednesday, June 4, 2025 / Categories: CASSATION, Cassation እነ አቶ አመድ ሙሜ(2ሰዎች)የእና ወ/ሮ አሚናት ኡስማንሰ/መ/ቁጥር 254020 ጉዳዩ የገጠር መሬት ውርስን የሚመለከት ሲሆን ጉዳዩ በጀመረበት የሀረሪ ህዝብ ክልላዊ መንግስት ከፍተኛ ፍ/ቤት የአሁን አመልካቾች ተከሳሽ፤ የአሁን ተጠሪ አውራሽ የሆኑት ወ/ሮ ከዲጃ ዑመር ከሳሽ ነበሩ፡፡ የአሁን ተጠሪ አውራሽ ያቀረቡት ክስም፡- ሟች አባታቸው በ1966 ዓ.ም በሞት የተለዩ መሆኑን፤ሟች አባታቸው እርሳቸውንና ሟች ወንድማቸውን አቶ ዘከሪያ ኡመር የወለዱ መሆኑን፤ሟች ወንድማቸውም የአሁን አመልካቾችን እናት አግብቶ ሲኖር ቆይቶ ልጅ ሳይወልድ እና ሳይናዝ የሞተ መሆኑን፤ ለክርክር መነሻ የሆነው በአራት ቦታ የሚገኘው የገጠር መሬት የሟች አባታቸው እና ክፍፍል ያልተፈጸመበት እንዲሁም ከሟች ወንድማቸው ጋር ሲጠቀሙበት የቆዩ መሆኑን፤ ሟች ወንድማቸው ከሞተ በኋላም የአሁን አመልካቾች እናት እየረዳቻቸው በመሬቱ ስትጠቀም እንደነበር፤ እርሷ ከሞተች በኋላ መሬቱን ተጠሪዎች እንዲለቁ ቢጠየቁ ፈቃደኛ ሊሆኑ አለመቻላቸውን ጠቅሰው መሬቱን ለቀው እንዲያስረክቡኝ እና ከመሬቱ የተገኘውን ጥቅም ጨምረው እንዲከፍሉኝ የሚል ነበር፡፡ ተጠሪዎች ለክሱ ባቀረቡት መልስ ክሱ በይርጋ የተቋረጠ ነው፡፡ ለክርክር መነሻ የሆነውን መሬት እናታችን መብት በመመስረት ንብረትነቱ የመንግስት በሆነ መሬት ላይ ከከሳሽ ወንድም ጋር ባልና ሚስት በመሆን ጋብቻው በሞት ቀሪ እስከሆነበት ጊዜ ድረስ መብት ፈጥረው እየተጠቀሙ የቆዩ በመሆኑ ክሱ ውድቅ እንዲደረግልን በማለት ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ…. Previous Article ጠቋሬ ፈለቀ እና አባ ምትኩ ዘዉዴ የሰ.መ.ቁ.253916 Next Article ቻይና ኮሙኒኬሽን ኩባንያ ግንባታ ወንጪ ደንዲ ኢኮቱሪዝም ፕሮጀክት እና ማንዴሳ ጪብሳ የሠ/መ/ቁጥር 256412 Print 4321 Documents to download 254020(.pdf, 832.14 KB) - 538 download(s)
በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እየተሰሩ ያሉ የለውጥ... በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እየተሰሩ ያሉ የለውጥ... Monday, June 8, 2026 78 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፕሬዝዳንትነትና ምክትል ፕሬዝዳንትነት ሲያገለግሉ የነበሩ የቀድሞ አመራሮች በፍርድ ቤቱ ተገኝተው አሁን ላይ እየተሰሩ ያሉ ዋና ዋና የለውጥ ስራዎችን በተመለከተ ውይይትና ምልከታ አድርገዋል። Read more
ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል የስራ ማስጀመሪያ... ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል የስራ ማስጀመሪያ... Thursday, May 28, 2026 97 በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት የተሰራ ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል (One way mirror) በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አዲስ ከተማ ምድብ ችሎት በይፋ ስራ ጀምሯል። Read more
ለሶሻል ወርክ ባለሞያዎች በተዘጋጀ የስልጠና ማንዋል ረቂቅ... ለሶሻል ወርክ ባለሞያዎች በተዘጋጀ የስልጠና ማንዋል ረቂቅ... Monday, May 25, 2026 119 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህፃናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት በፍትህ ስርዓት ውስጥ የሚያገለግሉ የማህበራዊ ሳይንስ ባለሞያዎችን ሚና ለማጎልበት የሚያግዝ የስልጠና ማንዋል የመጨረሻ ረቂቅ ሰነድ ላይ የውይይት እና የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ተካሂዷል፡፡ Read more
የኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፍተኛ ልዑካን ቡድን... የኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፍተኛ ልዑካን ቡድን... Thursday, May 21, 2026 106 በኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ እና የጄሲኢ (JCE) ሰብሳቢ በሆኑት በክብርት ዳኛ ሱዛን ኞኪ ንዱንጉ የተመራው ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ላለፉት ሦስት ተከታታይ ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር አጠናቋል። Read more
10Mar2026 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ የሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Tuesday, March 10, 2026 Read more