Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

እነ አቶ አበራ ነጋሽ ደምሴ(6) ሰዎች እና ቦሌ ቡልቡላ ደብረ መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን፤ የቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ፅ/ቤት የሰበር መ/ቁ/245981

ጉዳዩ የመሬት ባለይዞታነት መብት የሚመለከት ሲሆን በስር ፍርድ ቤት የአሁን አመልካቾች ከሳሽ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡አመልካቾች በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመ/ቁ131415 ባቀረቡት ክስ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ክልል ውስጥ የሚገኝ ከ1-5 የተዘረዘሩት አመልካቾች ወላጅ አባት እና የ6ኛ አመልካች ወንድም የሆኑት በጋራ ይዘው ይጠቀሙበት የነበረ በግምት ከ60‚000 ካ.ሜ ያላነሰ ስፋት ያለው አዋሳኞቹ በክሱ የተጠቀሰ ይዞታ ለረጅም ጊዜ ግብር እየገበሩበት ሲጠቀሙ የቆዩ ቢሆንም ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ በ1ኛ ተጠሪ ቤተክርስቲያን የሰበካ ጉባኤ ኮሚቴ አባላት አማካኝነት የሀይማኖት ተቋሙ በማህበረሰቡ ዘንድ ያለውን መፈራት እና መከበር በመጠቀም የአመልካቾችን ይዞታ ለመቃብር ቦታ በሚል ምክንያት በመውሰድ ከፋፍሎ እና ሼዶችን ገንብቶ ለጋራዥ እና ሌሎች የንግድ አገልግሎቶች ኪራይ ገቢ እየሰበሰበ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንዲሰራ በማድረግ በህገወጥ መንገድ ይዞት ይገኛል፡፡ስለሆነም ለ1ኛተጠሪ የተሰጠው የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ተሰርዞ ለአመልካቾች እንዲመለስ ሲሉ ዳኝነት መጠየቃቸዉን መዝገቡ ያሣያል፡፡መልካም ንባብ….

Previous Article አቶ ጉዕሽ ካሳ ደሞዝ እና እነ አቶ አማኑኤል ወልደሊባኖስ ተስፋዬ የሠ/መ/ቁጥር 243564
Next Article እነ አቶ ግርማ አዳነ እና ላልይበላ ንግድ ስራዎች ኃ/የተ/የግ/ማህበር የሰ/መ/ቁጥር 247702
Print
3993

Documents to download

  • 245981(.pdf, 942 KB) - 578 download(s)

«June 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
25262728293031
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
293012345

በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እየተሰሩ ያሉ የለውጥ...

78

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፕሬዝዳንትነትና ምክትል ፕሬዝዳንትነት ሲያገለግሉ የነበሩ የቀድሞ አመራሮች በፍርድ ቤቱ ተገኝተው አሁን ላይ እየተሰሩ ያሉ ዋና ዋና የለውጥ ስራዎችን በተመለከተ ውይይትና ምልከታ አድርገዋል።

ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል የስራ ማስጀመሪያ...

97

‎በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት የተሰራ ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል (One way mirror) በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አዲስ ከተማ ምድብ ችሎት በይፋ ስራ ጀምሯል።

ለሶሻል ወርክ ባለሞያዎች በተዘጋጀ የስልጠና ማንዋል ረቂቅ...

119

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህፃናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት በፍትህ ስርዓት ውስጥ የሚያገለግሉ የማህበራዊ ሳይንስ ባለሞያዎችን ሚና ለማጎልበት የሚያግዝ የስልጠና ማንዋል የመጨረሻ ረቂቅ ሰነድ ላይ የውይይት እና የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ተካሂዷል፡፡ 

‎የኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፍተኛ ልዑካን ቡድን...

106

በኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ እና የጄሲኢ (JCE) ሰብሳቢ በሆኑት በክብርት ዳኛ ሱዛን ኞኪ ንዱንጉ የተመራው ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ላለፉት ሦስት ተከታታይ ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር አጠናቋል።

1345678910Last