Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

እነ አቶ ዮሐንስ ገ/ሚካኤል(5ሰዎች) እና ወ/ሮ ሃና ደርሶልኝ(2ሰዎች) የሰበር መዝገብ ቁጥር - 256463

አመልካቾች ሚያዚያ 2 ቀን 2015 ዓ.ም በተፃፈ የመቃወም አቤቱታ ሟች አባታቸው አቶ ገ/ሚካኤል ኃ/ማርያም በህይወት እያሉ እንዲሁም አባታቸው ከሞቱ በኃላ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ የሆኑት፣ አመልካቾችና የ 96 አመት የሆኑት የግራ ቀኙ እናት ጋር በአልኮልና በለስላሳ ማከፋፈያ እንዲሁም በሸቀጣሸቀጦች ጅምላ ንግድ ስራ ተሰማርተው በቁጥር ስምንት የሆኑ የተለያዩ ተሸከርካሪዎች፤ ደምቢዶሎ ከተማ ውስጥ የሚገኝ ሆቴል፣ የቡና ማበጠሪያ፣ የመጠጥ ማከፋፈያ፣ የመኖሪያ ቤትና መጋዘን፤ በቡና ግብይት ላይ የነበረ አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሺህ ብር፣ በአዋሽ ባንክ ያለ 50 የአክስዮን ድርሻ በጋራ ያፈሩ መሆኑንና ተጠሪዎች ጋብቻ ሲፈፅሙ እነዚህ ንብረቶች የአመልካቾች መሆናቸውን በጋብቻ ውላቸው ተስማምተዋል፡፡ እነዚህ ንብረቶች ከፊሎቹ ባሉበት ከፊሎቹ በሽያጭ ሆነ በሌላ መንገድ እየተለዋወጡና እየተቀላቀሉ ብዛታቸው 16 የሆኑ በተጠሪ ስም የተመዘገቡ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች፤ በተጠሪ ስም የተመዘገቡ በአዋሽ ባንክ፣ በኦሮሚያ ባንክ፣ በህብረት ባንክ ያሉ አክስዮኖች፤ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ በአዋሽ ባንክ፣ በህብረት ባንክ፣ በኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ፣ በኦሮሚያ ባንክ ተጠራቅሞ የሚገኝ ገንዘብ እና ተሸከርካሪዎች በቤተሰብ የተፈሩና በተጠሪዎች የጋብቻ ውል ላይም የቤተሰብ ንብረቶች መሆናቸው ተረጋግጦ እያለ ተጠሪዎች ከዚህ በተቃራኒ በሰበታ ከተማ የሚገኘውን በ 612 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ቤት፣ በቄለም ወለጋ ዞን ደምቢዶሎ የሚገኘውን መኖሪያ ቤት እንዲሁም በዚህ ከተማ በ 2,000 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ሆቴል ን በመተው ሌሎችን ንብረቶች የተጠሪዎች የጋራ ንብረት ነው በማለት ያስወሰኑ በመሆኑ ውሳኔው ቀሪ እንዲሆን በማለት የመቃወም አቤቱታቸውን አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ…

Previous Article ቻይና ኮሙኒኬሽን ኩባንያ ግንባታ ወንጪ ደንዲ ኢኮቱሪዝም ፕሮጀክት እና ማንዴሳ ጪብሳ የሠ/መ/ቁጥር 256412
Next Article ወ/ሮ ሰላማዊት ያደሳ እነ አቶ ፀሀዬ ጌታቸው(2ሰዎች) የሠ/መ/ቁጥር 256923
Print
4723

Documents to download

  • 256463(.pdf, 853.95 KB) - 498 download(s)

«June 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
25262728293031
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
293012345

በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እየተሰሩ ያሉ የለውጥ...

0

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፕሬዝዳንትነትና ምክትል ፕሬዝዳንትነት ሲያገለግሉ የነበሩ የቀድሞ አመራሮች በፍርድ ቤቱ ተገኝተው አሁን ላይ እየተሰሩ ያሉ ዋና ዋና የለውጥ ስራዎችን በተመለከተ ውይይትና ምልከታ አድርገዋል።

ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል የስራ ማስጀመሪያ...

33

‎በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት የተሰራ ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል (One way mirror) በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አዲስ ከተማ ምድብ ችሎት በይፋ ስራ ጀምሯል።

ለሶሻል ወርክ ባለሞያዎች በተዘጋጀ የስልጠና ማንዋል ረቂቅ...

60

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህፃናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት በፍትህ ስርዓት ውስጥ የሚያገለግሉ የማህበራዊ ሳይንስ ባለሞያዎችን ሚና ለማጎልበት የሚያግዝ የስልጠና ማንዋል የመጨረሻ ረቂቅ ሰነድ ላይ የውይይት እና የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ተካሂዷል፡፡ 

‎የኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፍተኛ ልዑካን ቡድን...

58

በኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ እና የጄሲኢ (JCE) ሰብሳቢ በሆኑት በክብርት ዳኛ ሱዛን ኞኪ ንዱንጉ የተመራው ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ላለፉት ሦስት ተከታታይ ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር አጠናቋል።

1345678910Last