Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

እነ ወ/ሮ ተናኜ ሞላ ብርሐኔ(3ሰዎች) እና አቶ ሳሙኤል ተገኝ ኃይሌ የሰበር መዝገብ ቁጥር - 257774

ጉዳዩ የተጀመረው በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሲሆን በስር ፍርድ ቤት አመልካቾች ተጠሪዎች ተጠሪ ደግሞ አመልካች በመሆን ተከራክረዋል፡፡በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካቾች ላይ ያቀረቡት ክስ ይዘት በአጭሩ ወላጅ አባት ሟች አቶ ኃይሌ ተገኝ የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ኑዛዜ የፈፀሙ መሆኑን አመልካች የሟች ብቸኛ ልጅ መሆኑን ለተጠሪዎች ኑዛዜ በመፈፀም ከሚደርሰው ድርሻ ከሩብ በላይ ጉዳት እንዲደርስበት ያደረገ በመሆኑ ከኑዛዜው እንድነቀል ተደርጊያለሁ ስለዚህ ሟች ፈፀመውታል የተባለው ኑዛዜ እንዲሻርልኝ የሚል ነው፡፡

ከአመልካቾች በኩል የተሰጠው መልስ በአጭሩ ኑዛዜው በህግ ፊት የፀና ነው ሟች ማንም ሰው ሳያስገድዳቸው በራሳቸው ፍቃድና ፍላጎት በትክክለኛ አእምሮ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ ፊት ቀርበው የኑዛዜው ሰነድ ተነቦላቸው በምስክሮች ፊት የቁም ኑዛዜ ያደረጉ ስለሆነ ኑዛዜው ህጋዊ መሆኑን ሟች ጥር 29 ቀን 2012 ዓ.ም ባደረጉት የቁም ኑዛዜ በተራ ቁጥር 2፣ 3 እና 4 የተጠቀሱት የኑዛዜ ተቀባዮች በሟች ስም የሚጠሩ መሆናቸውን ኑዛዜ አድራጊው ልጆች ናቸው ብሎ የተቀበላቸውን ግለሰቦች 3ኛ ወገን ተወላጆች ስላልሆኑ የኑዛዜ ስጦታ ሊበረከትላቸው አይገባም ብሎ መከራከር የሟችን በንብረቱ ላይ የማዘዝ መብትን የሚጥስ በመሆኑ ተቀባይነት የሌለው መሆኑን የኑዛዜ ተቀባዮች ተወላጆች አይደሉም ቢባል እንኳን የኑዛዜ ስጦታ ለተወላጅ ብቻ የሚሰጥ መብት ነው የሚል የህግ ድንጋጌ ያለመኖሩን አመልካች ሟች አባታቸው ባደረጉት ኑዛዜ የኑዛዜ ተቀባይ ነው እንጂ በኑዛዜው ከውርስ አልተነቀለም፡፡ አመልካች ከጠየቁት ዳኝነት አንፃር በኑዛዜው የሚደርሳቸውን ድርሻ በትክክል ለይተው አልጠየቁም የሟች ቁም ኑዛዜ ፈራሽ የሚሆንበት በቂ ምክንያት ስላልቀረበ የአመልካች ክስ ውድቅ እንዲደረግ የሚል ነው፡፡መልካም ንባብ…  

Previous Article ወ/ሮ ሰላማዊት ያደሳ እነ አቶ ፀሀዬ ጌታቸው(2ሰዎች) የሠ/መ/ቁጥር 256923
Next Article አቶ መንገሻ መሮ እና እነ መ/ር መስፍን መንገሻ (2ሰዎች) የሰ/መ/ቁጥር 258429
Print
2920

Documents to download

  • 257774(.pdf, 891.93 KB) - 375 download(s)

«February 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
2627282930311
2345678
9101112131415
16171819202122
2324252627281
2345678

አዲስ ለተቀጠሩ ህግ ጉዳይ ጸሐፊ I እና የህግ ጉዳይ...

1

አዲስ ለተቀጠሩ ህግ ጉዳይ ጸሐፊ I እና የህግ ጉዳይ ጸሐፊ II በ ቀን 06 እና 09/06/2018 ዓ.ም የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አጠቃላይ ነባራዊ ሁኔታን እና ከለዉጥ ስራዎች ጋር ለማስተዋወቅ የመግቢያ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

ሥነ-ምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥና የጥቅም ግጭት መከላከልና...

6

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፌዴራል ሥነ-ምግባርና ፀረ -ሙስናና ኮሚሽን ጋር በመተባበር በሥነ-ምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥ እና የጥቅም ግጭት መከላከልና ማስተዳደር ላይ ከፍርድ ቤት ዘርፍ ለተውጣጡ የስራ ሃላፊዎች የካቲት 5 እና 6 ቀን 2018 ዓ.ም ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የኢትዮጵያ...

138

የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት እና የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ቢኒያም ኤሮ ናቸው፡፡

በዳኝነት ስርአቱ ውስጥ ለህጻናት ተስማሚ የፍትህ ስርአትን...

110

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት በዳኝነት ስርአት ውስጥ ለህጻናት ተስማሚ የፍትህ ስርአትን ለማጎልበት ከአጋር ድርጅቶች ጋር የጋራ ውይይት መድረክ በቀን 03/06/2018 ዓ.ም ተካሂዷል።

1345678910Last