Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

እነ ወ/ሮ ጌጤ ሙለታ(3ሰዎች) እና ወ/ሮ ብርሃኔ ካባ የሰ/መ/ቁ 249367

ለዚህ የሰበር አቤቱታ መቅረብ ምክንያት የሆነዉ ጉዳይ የዉርስ ክርክርን የሚመለከት ሆኖ ክርክሩ የተጀመረዉ በአምቦ ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን በወረዳዉ ፍርድ ቤት አመልካቾች ከሳሽ ተጠሪ ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ አመልካቾች በአምቦ ወረዳ ፍርድ ቤት በተጠሪ ላይ ባቀረቡት ክስ ሟች አባታቸዉን ሙለታ ካባን ተክተዉ ከሟች አያቶቻቸዉ አቶ ካባ ዳባ እና  ወ/ሮ ብርቱካን ፈካንሳ በዉርስ ሊያገኟቸዉ የሚገቡ በአምቦ ወረዳ ኢላሙ ጎርሚቲ ቀ/ገ/ማኅበር ዉስጥ በስድስት በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙትን የገጠር እርሻ ይዞታዎችን፣ በይዞታዎቹ ላይ የተፈሩ ቋሚ ሀብቶችንና የተለያዩ ከብቶችን ተጠሪ ከድርሻቸዉ በላይ ይዘዉ የሚገኙ መሆናቸዉን ገልፀዉ የዉርስ ሀብቶቹ ተጣርተዉ የሟች አባታቸዉን የዉርስ ድርሻ እንዲሁም ከፊሎቹ ከሳሾች ራሳቸዉን ችለዉ በጥገኝነት ሊያገኙ የሚገባቸዉን የዉርስ ድርሻ እንዲያገኙ እንዲወሰንላቸዉ ዳኝነት በመጠየቅ ክስ አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ…..

Previous Article ብርሃን ባንክ አ/ማ እና ብርሃን ባንክ መሠረታዊ የሠራተኞች ማሕበር የሰ/መ/ቁ. 263727
Next Article አቶ ኩማ መልኩ እና አቶ ሰለሞን ዘለቀ የሰበር መ/ቁ/250546
Print
2743

Documents to download

  • 249367(.pdf, 828.74 KB) - 355 download(s)

«January 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
2930311234
567891011
12131415161718
19202122232425
2627282930311
2345678

በአገልግሎት አሰጣጥና የተገልጋዩች አያያዝ ላይ ስልጠና ተሰጠ

7

ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰው ሃብት ስራ አመራር ዳይሬክተሮች፣ ቡድን መሪዎች፣ በሬጅስትራር ስር ላሉ እና ለሌሎች የአስተዳደር ዘርፍ ሰራተኞች ጥር 2 ቀን 2018 ዓ.ም በአገልግሎት አሰጣጥና የተገልጋዩች አያያዝ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል ፡፡

በፌዴራል ፍርድ ቤቶች በወንጀል ችሎት በሚታዩ ችግሮችና...

2

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፌዴራል ፍርድ ቤቶች በወንጀል ችሎቶች የሚታዩ ተግዳሮቶችና መፍትሔዎች ዙሪያ በተደረገ የዳሰሳ ጥናት ላይ ጥር 2 ቀን 2018 ዓ.ም የግብዓት ማሰባሰቢያ ዉይይት ተካሄዷል፡፡

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል...

1

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደዉ 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ስብሰባ በህገ-መንግስቱ አንቀጽ 81(2) መሰረት 34 የከፍተኛ ፍርድ ቤት እጩ ዳኞችን ሹመት አጽድቋል፡፡

የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞች በፌደራል...

1

የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞች በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ከቀን 21/04/2018 ዓ.ም እስከ 27/04/2018 ዓ.ም ለተከታታይ 5 የስራ ቀናት ጉብኝት እና ውይይት አድርገዋል፡፡

1345678910Last