Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

ወ/ሮ ሙርሽዳ ሁሴን እና ወ/ሮ አልፊያ ሁሴን (13) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 257243

ጉዳዩ የውርስ ንብረት እና የሚስትነት ድርሻ ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ጉዳዩ በጀመረበት በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት የአሁን አመልካች 1ኛ ጣ/ገብ ፤ከ1ኛ እስከ 5ኛ ያሉ ተጠሪዎች ከሳሽ፤ከ6ኛ እስከ 13ኛ ያሉ ተጠሪዎች እንዲሁ ጣ/ገብ አመልካች ነበሩ፡፡ አሁን ከ1ኛ እስከ 5ኛ ያሉ ተጠሪዎች አሁን በክርክሩ በሌሉ ሁለት ተከሳሾች ላይ ባቀረቡት ክስ የሟች አባታቸው አቶ ሁሴን አህመድ ንብረት የሆኑና በሟች ስም የሚገኙ 1ኛ/ በስር 1ኛ ተከሳሽ እጅ የሚገኝ በአሊቾ ውሪሮ ወረዳ ቀረሶ ቀበሌ ገሸዴ ተብሎ በሚጠራ መንደር የሚገኝ 3 ጥማድ የእርሻ መሬት፤2ኛ/ በስር 2ኛ ተከሳሽ እጅ የሚገኝ በወልቂጤ ከተማ 01 ቀበሌ የሚገኝ በ1050 ካ.ሜ ላይ ያለ የንግድ ቤት እና ከቤቱ የሚገኝ የኪራይ ገቢ፤3ኛ/ በስር 1ኛ ተከሳሽ እጅ የሚገኝ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 03-21138 የሆነ ዶልፊን ተሽከርካሪ፤ 4ኛ/ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና በደቡብ ግሎባል ባንክ በሟች ስም በተከፈቱ ሂሳቦች የተቀመጠ ገንዘብ የሟች የውርስ ሀብት ስለሆነ በድርሻችን ተከሳሾች ያካፍሉን ሲሉ ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ…

Previous Article ሆሆተ ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እናወ/ሮ ዘውዲቱ በዳሶ የሰ/መ/ቁ 256580
Next Article አቶ ተስፋዬ ደገፋ እና ዶ/ር ትዕዛዙ ተፈራ ፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ጽ/ቤት፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት የሰ/መ/ቁ 259947
Print
3936

Documents to download

  • 257243(.pdf, 868.34 KB) - 619 download(s)

«April 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
303112345
6789101112
13141516171819
20212223242526
27282930123
45678910

በኢትዮጵያ የአዘርባጃን አምባሳደር ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ...

19

በኢትዮጵያ የአዘርባጃን አምባሳደር እና የአፍሪካ አንድነት ቋሚ ተወካይ የተከበሩ ሩስላን ናሲቦቭ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተገኝተው በጋራ መስራት በሚቻል በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡

ሀገር አቀፍ የዳኝነት እና የፍትህ አካላት የጋራ መድረክ...

36

ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው አመታዊ ሀገር አቀፍ የዳኝነት እና የፍትህ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ (ጆይንድ አፕ ጀስቲስ ፎረም) የፌዴራልና የክልል የዳኝነትና የፍትህ አካላት የጋራ መድረክ የመግባቢያ ሰነድ የፊርማ ስነ ስርዓት በማከናወን ተጠናቋል።

የዳኝነትና የፍትህ አካላት በጋራ የሚመክሩበት፣...

20

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በመክፈቻ ንግግራቸው፤ የሕግ የበላይነት የተረጋገጠባት እና ፍትሕ የሰፈነባት ሀገር ከመገንባት አንጻር በጋራ ስራዎች ላይ ለመምከርና የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ የመድረኩ ሚና ከፍተኛ እንደሆነ በማንሳት፤ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በጋራ በመፍታት ተቋማዊም ሆነ የወል ግቦችን ማሳካት እንደሚቻል ገልጸዋል።

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ሰሚ ችሎት የወንጀል...

78

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከአውሮፓ ህብረት ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ሁለት የስልጠና ማኑዋሎች ማለትም ተከታታይ የወንጀል ችሎት አመራር ሥልጠና ማንዋል( Training Manual on continuous criminal trials )፣ ድንበር ተሻጋሪ እና ከባድ ወንጀሎች ሥልጠና ሞጁል(Training Module on Trans-Boundary and grave crimes) እንዲሁም "በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ሰሚ ችሎት የወንጀል ህግ ትርጉም ውሳኔዎች ስብስብ በጉዳዮች የተደራጁ ልዩ ዕትም" መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ.ም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የማስተዋወቅ ፕሮግራም አካሂዷል ፡፡

1345678910Last