Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

ወ/ሮ ኢየሩሳሌም ኃይሉ እና እነ ወ/ሮ እታገኘው ኃይሉ(4ሰዎች) የሰ/መ/ቁጥር 253718

ጉዳዩ የውርስ ማጣራትን ተከትሎ የውርስ ሀብት ስለመሆኑ በተለየ ንብረት ላይ መብት ያላቸው ወራሾች ሊያገኙ ይችሉ የነበረውን ገቢ ቤቱን ከያዘው ሰው ለመጠየቅ ያላቸውን መብት የሚመለከት ነው፡፡ክርክሩ የተጀመረው በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ሲሆን 1ኛ፣2ኛ እና 3ኛ ተጠሪዎች ከሳሾች፣4ኛተጠሪ ጣልቃገብ አንደዚሁም አመልካች ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡በተጠሪዎች የቀረበው ክስ በአጭሩ ሟቾች አቶ ሀይሉ ደነቀው እና ወ/ሮ ልንገርሽ ይሁኔ በ422 ካ.ሜ ላይ ያረፈና የቤት ቁጥር 191 የሆነ ዋና ቤትና ሰርቪስ ቤቶች የነበሯቸው ሲሆን በመ/ቁ 82464 በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት መናገሻ ምድብ ችሎት በነበረን የውርስ ሀብት ይጣራልን ክርክር ላይ የሟች አቶ ኃይሉ ደነቀው የውርስ ሀብት ተጣርቶ ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡አመልካች በኑዛዜ የተላለፈላቸው 02 ክፍል ቤት ብቻ ሲሆን ክፍሎቹን እያከራዩ የሚጠቀሙበት ሆኖ በውርስ የሚደርሰንን ዋና ቤትና ሰርቪስ ቤቶችን ከህግ አግባብ ውጪ በመያዝ በዋናው ቤት እየኖሩበት አከራይተን እንዳንጠቀም በማድረግ ሰርቪስ ቤቶቹን ከተከራዩት ሰዎች ላይ የኪራዩን ገንዘብ በመሰብሰብ ለራሳቸው ጥቅም በማዋል ልናገኝ የሚገባውን ጥቅም አሳጥተውናል፡፡በመሆኑም በውሳኔው መሰረት የሚኖሩበትን ዋናውን ባለ ሶስት ክፍሉን ቤት እና የምያከራዩትን 03 ክፍል ሰርቪስ ቤቶች ከነቦታው ለቀው እንዲያስረክቡን በተደጋጋሚ ከመጠየቅ ባሻገር ጥቅምት 29 ቀን 2014 ዓ.ም ደግሞ የጹሑፍ ማስጠንቀቂያ የሰጠናቸው ቢሆንም አመልካች ቤቶቹን ለማስረከብ እንደዚሁም የቤቶቹ ኪራይ ገንዘብ ለመክፈል ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሟች ከሞቱበት ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ ዋናው ቤት ቢከራይ በወር ብር 8000 (ስምንት ሺህ) ክስ እስካቀረብንበት ጊዜ ድረሰ ያለውን የ28 ወር ብር 224,000.00 (ሁለት መቶ ሀያ አራት ሺህ) እንዲከፍሉን፣የሚከራዩ 3 (ሶስት) ክፍል ሰርቪስ ቤቶች ሟች ከሞቱበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ሚያዚያ ወር ብር 1500 (አንድ ሺ አምስት መቶ) ይከራይ የነበረው አመልካች ብር 300 (ሶስት መቶ) በመጨመር ብር 1800 (አንድ ሺ ስምንት መቶ)፣ ሌላው 1 (አንድ) ክፍል ቤት 500 (አምስት መቶ) ይከራይ ነበረው ብር 700 (ሰባት መቶ) እና ቀሪውን 01 ክፍል ቤት በብር 1000 (አንድ ሺህ) ልዩነቱ የ4 (አራት) ወር ብር 4000 (አራት ሺ)  ሟች ከሞቱበት ጊዜ ጀምሮ እስከ መጋቢት ወር መጨረሻ ክስ እስካቀረብንበት ጊዜ ድረስ ያለው ሲሰላ ሁለት ዓመት 24 (ሀያ አራት) ወር በመሆኑ ብር 70,000.00 (ሰባ ሺህ) በድምሩ ብር 74,000 (ሰባ አራት ሺህ) ልናገኝ የሚገባውን ጥቅም ያሳጡን ስለሆነ ዋናውን ቤት እና የሰርቪስ ቤቶቹን የኪራይ ገንዘብ ተከፍሎ እስከሚጠናቀቅበት ድረስ ከነወለዱ ታስቦ እንድከፍሉን እንዲወሰንልን የሚል ነው፡፡መልካም ንባብ…..

Previous Article ሐረማያ ዩንቨርስቲ እና መላ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግል ማሕበር የሰ/መ/ቁ. 253530
Next Article ወ/ሮ ሳፊያ ከድር እና እነ ሐጂ አማን ሐጂ ሁሴን (6ሰዎች) የሠ/መ/ቁጥር 254696
Print
3453

Documents to download

  • 253718(.pdf, 1.07 MB) - 438 download(s)

«March 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
2324252627281
2345678
9101112131415
16171819202122
23242526272829
303112345

የዳኝነትና የዴሞክራሲ ተቋማት እምርታ፤ ለሀገረ መንግስት...

154

የካቲት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ''የዳኝነትና የዴሞክራሲ ተቋማት እምርታ ለተሳካ ሀገረ መንግሥት ግንባታ" በሚል መሪ ቃል በዳኝነትና የዴሞክራሲ ተቋማት የለውጥ ስራዎች ላይ በማተኮር ሲካሄድ የቆየው የምክክር መድረክ ተጠናቋል።

ከምርጫ ጉዳዮች ጋር በተያያዙ ቅሬታዎች እና አፈታት ላይ...

220

ከምርጫ ጉዳዮች ጋር በተያያዙ ቅሬታዎች እና አፈታት ላይ ለፌዴራል እና ለክልል ዳኞች ከቀን 09/06/2018 ዓ.ም ጀምሮ በ3 ዙር ለ9 ቀናት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና በቀን18/5/2018 ዓ.ም ተጠናቀቀ፡፡

በአለምአቀፍ ወንጀሎች ዙሪያ ለፌዴራል ጠቅላይ እና...

119

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከዳኒሽ ኢንቲትዩት ፎር ሁማን ራይትስ ጋር በመተባበር ከፌዴራል ጠቅላይ እና ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለተውጣጡ ዳኞች በአለምአቀፍ ወንጀሎች ዙሪያ በስድስት የስልጠና ርእሶች በተከታታይነት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና የማጠናቀቂያ መርሐግብር የካቲት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ተካሂዷል።

1345678910Last