የሰበሶራ ሴኪዩሪቲ ኃ/የተ/የግ/ማ እና ታቦር ሴራሚክስ ውጤቶች አ/ማህበር የሰ/መዝገብ ቁጥር -253253
ጉዳዩ የተጀመረው በሲዳማ ብሄራዊ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ የስር ከሳሽ በተከሳሽ ላይ ያቀረበው ክስ ይዘቱ በአጭሩ የፋብሪካውን ደህንነት ለማስጠበቅ የጥበቃ ውል ከተከሳሽ ጋር በ02/05/2014 ዓ.ም መፈፀሙን ተከሳሽ ግዴታውን ባለመወጣት በተለያዩ ጊዜ የከሳሽ ንብረት የተሰረቀ በመሆኑ የንብረቱ ግምት ብር 4,825,295.00 (አራት ሚሊዮን ስምንት መቶ ሃያ አምስት ሺህ ሁለት መቶ ዘጠና አምስት ብር) ጉዳት ያደረሰ በመሆኑ በፍ/ብ/ህ አንቀፅ 2028 መሰረት እንዲከፍል የሚል ነው፡፡ ከተከሳሽ በኩል ለክሱ የተሰጠው መልስ ይዘቱ በአጭሩ ከሳሽ ተሰረቀብኝ ብሎ ያቀረበው 38 ዕቃ በውላችን መሰረት ተቆጥሮ ያልተሰጠ ንብረት በመሆኑ በተከሳሽ ጥፋት ጉዳት አልደረሰበትም፡፡ ጠፉ ከተባሉት ንብረቶች ውስጥ በውላችን አንቀፅ 4.2 መሰረት ያልተረከብኩትና የማላውቀው ነው፡፡ ተሰረቀ ከማለት ውጪ ከየትኛው መጋዘን እንደተሰረቀ እና የትኛው እቃ እንደተሰረቀ በስማቸው ዘርዝሮ አለማቅረቡ እቃዎቹ አለመሰረቃቸውን የሚያሳይ ከመሆኑ በተጨማሪ በተለያዩ ቦታ ላይ እርስ በርስ የሚጋጭ የዋጋ ዝርዝር አቅርቧል፡፡ የጠቀሳቸው እቃዎች ለመያዝ ፍቃድ የለውም፡፡ በስርቆት ጥርጣሬ በተደረገ ቆጠራ የከሳሽ ሰራተኞች በኦዲት ይጠየቃሉ እንጂ ከውጪ እየጠበቁ ያሉ ጥበቃዎች ተጠያቂ ሊሆኑ የሚችሉበት አግባብ ስለሌለ ተከሳሽ ለከሳሽ የሚከፍለው ገንዘብ የለም ተብሎ እንዲወሰን የሚል መልስ ከሰጡ በኃላ የተከሳሽ ከሳሽነት ክስ አቅርቧል፡፡ ዝርዝሩ በአጭር ከሳሽ ጠፍቶብኛል በሚል ምክንያት በመካከላችን ያለውን ውል በ28/01/2014 ዓ.ም አቋርጦ ያለበትን ውዝፍ ደመወዝ የ 10 ወር 834,652.21 (ስምንት መቶ ሰላሳ አራት ሺህ ስድስት መቶ ሃምሳ ሁለት ብር ከሃያ አንድ ሳንቲም) በተጨማሪ ለተመደቡ ለአራት ጥበቃዎች የ 6 ወር ብር 55,643.47 (ሃምሳ አምስት ሺህ ስድስት መቶ አርባ ሶስት ብር ከአርባ ሰባት ሳንቲም) በውላችን መሰረት ያለማስጠንቀቂያ ውሉን በማቋረጡ ብር 92,739.12 ውል ለማፍረሱ ቅጣት 5,000.00 ብር በአጠቃላይ ብር 990,816.23 (ዘጠኝ መቶ ዘጠና ሺህ ስምንት መቶ አስራ ስድስት ብር ከሃያ ሶስት ሳንቲም) ከሳሽ ለተከሳሽ እንዲከፍል የሚል ነው፡፡መልካም ንባብ…
4381
Documents to download
-
253253(.pdf, 836.43 KB) - 489 download(s)