ደጀኔ ደበላ አልቀረበም እና ኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 251700
ጉዳዩ ይለፍ ወረቀት ሳይይዙ የግብርና ምርቶችን ማጓጓዝ ወንጀል የሚመለከት ነው፡፡ክርክሩ የተጀመረው በሰሜን ሸዋ ዞን ወራ ጃርሶ ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን ተጠሪ ከሳሽ አመልካች ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡በተጠሪ የቀረበውም ክስ አመልካች የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ያወጣውን የገበያ ቁጥጥርና የምርት ጥራት አዋጅ ቁጥር 234/2013 አንቀፅ 26(3) እና 5 በመተላለፍ ታህሳስ 03 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ በግምት 4፡00 ሰአት በወራ ጃርሶ ወረዳ ቀሬ ጎሃ ከተማ ቀበሌ 02 ልዩ ቦታው ኬላ ተብሎ በሚጠራዉ ቦታ የሰሌዳ ቁጥር 3-16932 ኢት በሆነ ሲኖ ትራክ ተሽከርካሪ ላይ 220(ሁለት መቶ ሃያ) ኩንታል ባቄላ ግምቱ 836,000 (ስምንት መቶ ሰላሳ ስድስት ሺህ) የሆነውን ከአዲስ አበባ ወደ አማራ ክልል አቅጣጫ በመጓዝ ላይ እያለ ከላይ በተጠቀሰው ቦታ ሲደርስ በኬላ ተቆጣጣሪዎች ሲፈተሽ የንግድ ፍቃዱና የመነሻ እና መድረሻ የይለፍ ወረቀት ሳይይዝ በመጓዙ ያለ ፍቃድ የግብር ምርቶችን በማጓጓዝ ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡መልካም ንባብ…..
2661
Documents to download
-
251700(.pdf, 881.19 KB) - 314 download(s)