Selam Warga / Tuesday, June 17, 2025 / Categories: CASSATION, Cassation አቶ ኃይለ ጊዮርግስ ይልማ ወልደአብ እና እነ አቶ አዲስ እሸቱ (4) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 252056 ለዚህ የሰበር አቤቱታ ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን በወረዳዉ ፍርድ ቤት 1ኛ ተጠሪ ከሳሽ የአመልካች አዉራሽ ሟች አቶ ይልማ ወልደአብና ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ 1ኛ ተጠሪ በጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተራ ቁጥር ላይ በተጠቀሱት ተጠሪዎችና በአመልካች አባት በሟች አቶ ይልማ ወልደአብ ላይ ባቀረቡት ክስ በክሱ ላይ አዋሳኞቹ የተመለከተዉን 400 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈዉን የመኖሪያ ቤት ከነሰርቪስ ቤቶቹ ጭምር የካቲት 27 ቀን 2011 ዓ/ም በተፈረመ የሽያጭ ዉል ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (ከሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) በብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ) ገዝተዉ ካርታ በስማቸዉ የተሰጣቸዉ ቢሆንም በይዞታዉ ላይ ካሉ ቤቶች መካከል አንዱን የአመልካች ወላጅ አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) ይዘዉ ለመልቀቅ ፈቃደኛ አለመሆናቸዉን ገልፀዉ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (የሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) የሸጡላቸዉን ቤት ከአመልካች አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) አስለቅቀዉ እንዲያስረክቡና የአመልካች አባትም (የሥር 4ኛ ተከሳሽም) መብት ሳይኖራቸዉ የያዙትን የ1ኛ ተጠሪን (የሥር ከሳሽን) ቤት ለቀዉ እንዲወጡ እንዲወሰንላቸዉ ዳኝነት በመጠየቅ ክስ አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ…. Previous Article የፌደራል ዐቃቤ ህግ እና አቶ አበበ ወንድሙ ኤጋ የሰ/መ/ቁጥር 251759 Next Article የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አቶ መጣልኝ መላኩ የሰ.መ.ቁ.252953 Print 1827 Documents to download 252056(.pdf, 838.15 KB) - 258 download(s)
በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የለማ የኢፋይሊንግ፣... በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የለማ የኢፋይሊንግ፣... Monday, May 26, 2025 533 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የለማ በፍርድ ቤቶችና በማረሚያ ቤት መካከል ታራሚዎችን ለመፍታት የሚያስችል የመፈቻ ትዕዛዝ የሚላክበት የቴክኖሎጂ መተግበሪያ የሆነው የኢፋይሊንግ፣ ኢሊቲጌሽንና ሰነድ ልውውጥ ሲስተም ላይ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የፌደራል ማረሚያ ቤት አመራሮች እንዲሁም የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በቀን 15/09/2017 ዓ.ም የግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይት ተካሄደ። Read more
የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር... የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር... Wednesday, May 21, 2025 728 የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ክልላዊ ዳይሬክተር (The office of the United Nations High Commissioner for Human Rights (OHCHR) regional director) ሚስተር ማርሴል አክፖቮ እና ልዑክ ቡድናቸው በቀን 12/09/2017 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ውይይት እና የስራ ጉብኝት አድርገዋል፡፡ Read more
ለፌደራል ፍርድ ቤቶች መካከለኛ አመራሮች እና ሰራተኞች... ለፌደራል ፍርድ ቤቶች መካከለኛ አመራሮች እና ሰራተኞች... Tuesday, May 6, 2025 581 በፌደራል ፍርድ ቤቶች እየተተገበሩ የሚገኙ የለውጥ ሥራዎችን ተፈጻሚ ለማድረግ እንዲረዳ ከሶስቱም ደረጃ የፌደራል ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ ዳይሬክተሮች፣ ቡድን መሪዎች፣ መካከለኛ አመራሮች እና ሌሎች ሰራተኞች የተሳተፉበት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በስድስት ዙሮች በመስጠት ተጠናቀቀ፡፡ Read more
የፌደራል የወንጀል ፍትህ አስተዳደር አብይ ኮሚቴ የውይይት... የፌደራል የወንጀል ፍትህ አስተዳደር አብይ ኮሚቴ የውይይት... Tuesday, April 29, 2025 623 የፌደራል ፍትህ ተቋማት አመራሮች የተገኙበት የፌደራል የወንጀል ፍትህ አስተዳደር አብይ ኮሚቴ የውይይት መድረክ በቀን 21/08/2017 ዓ.ም ተካሂዷል። Read more
6Nov2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ ሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Thursday, November 6, 2025 Read more
8Oct2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ ሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Wednesday, October 8, 2025 Read more