Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ኃይለ ጊዮርግስ ይልማ ወልደአብ እና እነ አቶ አዲስ እሸቱ (4) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 252056

ለዚህ የሰበር አቤቱታ ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን በወረዳዉ ፍርድ ቤት 1ኛ ተጠሪ ከሳሽ የአመልካች አዉራሽ ሟች አቶ ይልማ ወልደአብና ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ 1ኛ ተጠሪ በጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተራ ቁጥር ላይ በተጠቀሱት ተጠሪዎችና በአመልካች አባት በሟች አቶ ይልማ ወልደአብ ላይ ባቀረቡት ክስ በክሱ ላይ አዋሳኞቹ የተመለከተዉን 400 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈዉን  የመኖሪያ ቤት ከነሰርቪስ  ቤቶቹ ጭምር የካቲት 27 ቀን 2011 ዓ/ም በተፈረመ የሽያጭ ዉል ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (ከሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) በብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ) ገዝተዉ ካርታ በስማቸዉ የተሰጣቸዉ ቢሆንም በይዞታዉ ላይ ካሉ ቤቶች መካከል አንዱን የአመልካች ወላጅ አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) ይዘዉ ለመልቀቅ ፈቃደኛ አለመሆናቸዉን ገልፀዉ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (የሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) የሸጡላቸዉን ቤት ከአመልካች አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) አስለቅቀዉ እንዲያስረክቡና የአመልካች አባትም (የሥር 4ኛ ተከሳሽም) መብት ሳይኖራቸዉ የያዙትን የ1ኛ ተጠሪን (የሥር ከሳሽን) ቤት ለቀዉ እንዲወጡ እንዲወሰንላቸዉ ዳኝነት በመጠየቅ ክስ አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ….

Previous Article የፌደራል ዐቃቤ ህግ እና አቶ አበበ ወንድሙ ኤጋ የሰ/መ/ቁጥር 251759
Next Article የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አቶ መጣልኝ መላኩ የሰ.መ.ቁ.252953
Print
1827

Documents to download

  • 252056(.pdf, 838.15 KB) - 258 download(s)

«November 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
1234567

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የለማ የኢፋይሊንግ፣...

533

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የለማ በፍርድ ቤቶችና በማረሚያ ቤት መካከል ታራሚዎችን ለመፍታት የሚያስችል የመፈቻ ትዕዛዝ የሚላክበት የቴክኖሎጂ መተግበሪያ የሆነው የኢፋይሊንግ፣ ኢሊቲጌሽንና ሰነድ ልውውጥ ሲስተም ላይ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የፌደራል ማረሚያ ቤት አመራሮች እንዲሁም የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በቀን 15/09/2017 ዓ.ም የግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይት ተካሄደ።

የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር...

728

የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ክልላዊ ዳይሬክተር (The office of the United Nations High Commissioner for Human Rights (OHCHR) regional director) ሚስተር ማርሴል አክፖቮ እና ልዑክ ቡድናቸው በቀን 12/09/2017 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ውይይት እና የስራ ጉብኝት አድርገዋል፡፡

ለፌደራል ፍርድ ቤቶች መካከለኛ አመራሮች እና ሰራተኞች...

581

በፌደራል ፍርድ ቤቶች እየተተገበሩ የሚገኙ የለውጥ ሥራዎችን ተፈጻሚ ለማድረግ እንዲረዳ ከሶስቱም ደረጃ የፌደራል ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ ዳይሬክተሮች፣ ቡድን መሪዎች፣ መካከለኛ አመራሮች እና ሌሎች ሰራተኞች የተሳተፉበት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በስድስት ዙሮች በመስጠት ተጠናቀቀ፡፡

First89101113151617Last