Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ኃይለ ጊዮርግስ ይልማ ወልደአብ እና እነ አቶ አዲስ እሸቱ (4) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 252056

ለዚህ የሰበር አቤቱታ ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን በወረዳዉ ፍርድ ቤት 1ኛ ተጠሪ ከሳሽ የአመልካች አዉራሽ ሟች አቶ ይልማ ወልደአብና ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ 1ኛ ተጠሪ በጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተራ ቁጥር ላይ በተጠቀሱት ተጠሪዎችና በአመልካች አባት በሟች አቶ ይልማ ወልደአብ ላይ ባቀረቡት ክስ በክሱ ላይ አዋሳኞቹ የተመለከተዉን 400 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈዉን  የመኖሪያ ቤት ከነሰርቪስ  ቤቶቹ ጭምር የካቲት 27 ቀን 2011 ዓ/ም በተፈረመ የሽያጭ ዉል ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (ከሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) በብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ) ገዝተዉ ካርታ በስማቸዉ የተሰጣቸዉ ቢሆንም በይዞታዉ ላይ ካሉ ቤቶች መካከል አንዱን የአመልካች ወላጅ አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) ይዘዉ ለመልቀቅ ፈቃደኛ አለመሆናቸዉን ገልፀዉ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (የሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) የሸጡላቸዉን ቤት ከአመልካች አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) አስለቅቀዉ እንዲያስረክቡና የአመልካች አባትም (የሥር 4ኛ ተከሳሽም) መብት ሳይኖራቸዉ የያዙትን የ1ኛ ተጠሪን (የሥር ከሳሽን) ቤት ለቀዉ እንዲወጡ እንዲወሰንላቸዉ ዳኝነት በመጠየቅ ክስ አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ….

Previous Article የፌደራል ዐቃቤ ህግ እና አቶ አበበ ወንድሙ ኤጋ የሰ/መ/ቁጥር 251759
Next Article የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አቶ መጣልኝ መላኩ የሰ.መ.ቁ.252953
Print
1833

Documents to download

  • 252056(.pdf, 838.15 KB) - 259 download(s)

«November 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
1234567

በስዊድን የልምድ ልውውጥ ያደረጉ የፌደራል ዳኞች ከሶስቱም...

774

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ከ UNODC (United Nations I Office on Drugs and Crime) ጋር በመተባበር ባዘጋጀው መድረክ በስዊድን አገር የልምድ ልውውጥ አድርገው የተመለሱ የፌደራል ዳኞች ከሶስቱም ፍርድ ቤት ለተውጣጡ ዳኞች ልምዳቸውን አካፍለዋል።

የUNODC (United Office on Drugs and...

822

የUNODC (United Office on Drugs and crime) የምስራቅ አፍሪካ ተወካይ ሚስ አሺታ ሚታል ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ጋር በቀን 30/07/2017 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ውይይት አድርገዋል፡፡

ሰባተኛ ዙር የፌደራል ፍርድ ቤቶች ጉባኤ ተካሔደ

617

የፌደራል ፍርድ ቤቶች ፕሬዝደንቶች፣ ምክትል ፕሬዝደንቶች፣የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ዳኞች፣ የፌደራል ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ተወካይ ዳኞች፣ የክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝደንቶች፣የአዲስ አበባና የድሬዳዋ ከተማ ፍርድ ቤቶች ፕሬዝደንቶችን በአባልነት ያቀፈው ሰባተኛ ዙር የፌደራል ፍርድ ቤቶች ጉባኤ መጋቢት 28 ቀን 2017 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ ተካሂዷል፡፡

በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ሲካሄድ የቆየው ሀገር...

507

በመድረኩም ከተመረጡ አጀንዳዎች ጋር በተገናኘ ሙያዊ ማብራሪያዎች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በመጨረሻም ለመጪው 1 ዓመት የግንኙነት መድረኩ ምክትል ሰብሳቢ ምርጫ ተደርጎ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ኤርሴኖ አቡሬ ተመርጠዋል።

First910111214161718Last