Selam Warga / Tuesday, June 17, 2025 / Categories: CASSATION, Cassation አቶ ኃይለ ጊዮርግስ ይልማ ወልደአብ እና እነ አቶ አዲስ እሸቱ (4) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 252056 ለዚህ የሰበር አቤቱታ ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን በወረዳዉ ፍርድ ቤት 1ኛ ተጠሪ ከሳሽ የአመልካች አዉራሽ ሟች አቶ ይልማ ወልደአብና ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ 1ኛ ተጠሪ በጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተራ ቁጥር ላይ በተጠቀሱት ተጠሪዎችና በአመልካች አባት በሟች አቶ ይልማ ወልደአብ ላይ ባቀረቡት ክስ በክሱ ላይ አዋሳኞቹ የተመለከተዉን 400 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈዉን የመኖሪያ ቤት ከነሰርቪስ ቤቶቹ ጭምር የካቲት 27 ቀን 2011 ዓ/ም በተፈረመ የሽያጭ ዉል ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (ከሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) በብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ) ገዝተዉ ካርታ በስማቸዉ የተሰጣቸዉ ቢሆንም በይዞታዉ ላይ ካሉ ቤቶች መካከል አንዱን የአመልካች ወላጅ አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) ይዘዉ ለመልቀቅ ፈቃደኛ አለመሆናቸዉን ገልፀዉ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (የሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) የሸጡላቸዉን ቤት ከአመልካች አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) አስለቅቀዉ እንዲያስረክቡና የአመልካች አባትም (የሥር 4ኛ ተከሳሽም) መብት ሳይኖራቸዉ የያዙትን የ1ኛ ተጠሪን (የሥር ከሳሽን) ቤት ለቀዉ እንዲወጡ እንዲወሰንላቸዉ ዳኝነት በመጠየቅ ክስ አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ…. Previous Article የፌደራል ዐቃቤ ህግ እና አቶ አበበ ወንድሙ ኤጋ የሰ/መ/ቁጥር 251759 Next Article የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አቶ መጣልኝ መላኩ የሰ.መ.ቁ.252953 Print 1833 Documents to download 252056(.pdf, 838.15 KB) - 259 download(s)
በስዊድን የልምድ ልውውጥ ያደረጉ የፌደራል ዳኞች ከሶስቱም... በስዊድን የልምድ ልውውጥ ያደረጉ የፌደራል ዳኞች ከሶስቱም... Monday, April 14, 2025 774 የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ከ UNODC (United Nations I Office on Drugs and Crime) ጋር በመተባበር ባዘጋጀው መድረክ በስዊድን አገር የልምድ ልውውጥ አድርገው የተመለሱ የፌደራል ዳኞች ከሶስቱም ፍርድ ቤት ለተውጣጡ ዳኞች ልምዳቸውን አካፍለዋል። Read more
የUNODC (United Office on Drugs and... የUNODC (United Office on Drugs and... Wednesday, April 9, 2025 822 የUNODC (United Office on Drugs and crime) የምስራቅ አፍሪካ ተወካይ ሚስ አሺታ ሚታል ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ጋር በቀን 30/07/2017 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ውይይት አድርገዋል፡፡ Read more
ሰባተኛ ዙር የፌደራል ፍርድ ቤቶች ጉባኤ ተካሔደ ሰባተኛ ዙር የፌደራል ፍርድ ቤቶች ጉባኤ ተካሔደ Tuesday, April 8, 2025 617 የፌደራል ፍርድ ቤቶች ፕሬዝደንቶች፣ ምክትል ፕሬዝደንቶች፣የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ዳኞች፣ የፌደራል ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ተወካይ ዳኞች፣ የክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝደንቶች፣የአዲስ አበባና የድሬዳዋ ከተማ ፍርድ ቤቶች ፕሬዝደንቶችን በአባልነት ያቀፈው ሰባተኛ ዙር የፌደራል ፍርድ ቤቶች ጉባኤ መጋቢት 28 ቀን 2017 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ ተካሂዷል፡፡ Read more
በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ሲካሄድ የቆየው ሀገር... በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ሲካሄድ የቆየው ሀገር... Tuesday, April 8, 2025 507 በመድረኩም ከተመረጡ አጀንዳዎች ጋር በተገናኘ ሙያዊ ማብራሪያዎች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል። በመጨረሻም ለመጪው 1 ዓመት የግንኙነት መድረኩ ምክትል ሰብሳቢ ምርጫ ተደርጎ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ኤርሴኖ አቡሬ ተመርጠዋል። Read more
6Nov2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ ሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Thursday, November 6, 2025 Read more
8Oct2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ ሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Wednesday, October 8, 2025 Read more