Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
2641

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 481 download(s)

«November 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
1234567

ሀገር አቀፍ የህግ ተርጓሚዎች መድረክ እየተካሄደ ይገኛል

624

የፌደራል እና የክልል ፍርድ ቤቶች ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንቶችን ያካተተ ሀገር አቀፍ የህግ ተርጓሚዎች መድረክ በቀን 27/07/2017 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ላይ የሁለት ቀናት ስልጠና ተሰጠ

679

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፌደራል የፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት እና ከኢትዮጵያ የማስማማትና ግልግል ዳኝነት ማዕከል (EMAC) ጋር በመተባበር የሁለት ቀናት ስልጠና ለፌደራል ከፍተኛ እና መጀመሪያ ፍርድ ቤት ረዳት ዳኞች ተሰጥቷል፡፡

ስዊድን አገር ለተደረገው የስራ ጉብኝትና ልምምድ ልውውጥ...

498

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከአውሮፓ ህብረት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እያከናወነ ከሚገኘው የወንጀል ፍትህ አስተዳደር መሻሻያ ተግባራት መካከል በወንጀል ፍትህ አስተዳደር የተሻለ ተሞክሮ ካላቸው አውሮፓ አገራት ፍርድ ቤቶች ልምድ መቅሰም ይገኝበታል። ይህንኑ ተከትሎ በቅርቡ 23 የፌደራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች ወደ ስዊድን አገር በመጓዝ ከአገሪቱ ፍ/ቤቶች ልምምድ መቅሰማቸው ይታወቃል፡:

First1011121315171819Last