Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
2641

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 481 download(s)

«November 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
1234567

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት የአንድ...

522

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት እና በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለሚ ኩራ ምድብ ችሎት በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል።

የፍርድ ቤት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ መልካም ስነ ምግባርን...

671

በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መልካም ስነ-ምግባራዊ ባህርይ የተላበሰ አገልግሎት አሰጣጥን ለማጎልበት ስነልቦና፣ ስነምግባርና አገልግሎት አሰጣጥ በሚል ርዕስ መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከተቋሙ ልዩ ልዩ የስራ ክፍሎች ለተዉጣጡ 115 ሰራተኞች ተሰጥቷል፡፡

የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ማሻሻያ ረቂቅ ላይ...

531

ላለፉት አስራ አንድ ዓመታት በሥራ ላይ የቆየውን የፍርድ ቤቶች የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ለማሻሻል ተዘጋጅቶ በቀረበ ረቂቅ መመሪያ ላይ ግብአት ለማሰባሰብ የተዘጋጀና የፌደራል ፍርድ ቤቶችን ጨምሮ ከሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ጥሪ የተደረገላቸው 160 ያህል ዳኞች፣ ዐቃቢያነ ሕግ፣ ጠበቆች እና ሌሎች የሕግ ባለሙያዎች የተሳተፉበት የምክክር መድረክ የካቲት 29 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሔደ፡፡

በከባድና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ላይ የተዘጋጀ ሥልጠና...

550

ለፌደራል ፍርድ ቤቶች እና ከሁሉም ክልል ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ ዳኞች እንዲሁም ለወታደራዊ ፍርድ ቤት ዳኞች በከባድና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ላይ የተዘጋጀ የአንድ ቀን ስልጠና የካቲት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሄደ፡፡

First1112131416181920Last