Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
4337

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 677 download(s)

«February 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
2627282930311
2345678
9101112131415
16171819202122
2324252627281
2345678

የሰበር ሰርዓትን ማጠናከር ለዳኝነት ሪፎርም በሚል የቀረበ...

893

የሰበር ሰርዓትን ማጠናከር ለዳኝነት ሪፎርም(Strengthening the cassation system for effective judicial reform) በሚል የቀረበ ጽሁፍ ላይ በቀን 27/11/2017 ዓ.ም የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፍተኛ አመራሮችና ዳኞች በተገኙበት ውይይት ተደርጓል፡፡

ለኢትዮጵያ አይነስውራን ብሔራዊ ማሕበር ጽ/ቤት የሰበር...

732

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሕትመት ተዘጋጅተው ከቅጽ 19-26 የወጡ የሰበር ውሳኔዎችን በድምጽ ቅጂ እንዲዘጋጁ በማድረግ ለኢትዮጵያ አይነስውራን ብሔራዊ ማሕበር ጽ/ቤት ሐምሌ 23 ቀን 2017 ዓ.ም አበረከተ፡፡

የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ...

891

የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ለቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ዝርጋታ ላደረገው አስተዋጽኦ፣ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የኢንፎርሜሽንና ኮሚዩኒኬሽን ክፍል ሃላፊና ባለሙያዎች ላደረጉት ድጋፍ የእውቅና ምስክር ወረቀት አበርክቷል፡፡

First1213141517192021Last