Selam Warga / Tuesday, June 17, 2025 / Categories: CASSATION, Cassation አቶ ተስፋዬ ደገፋ እና ዶ/ር ትዕዛዙ ተፈራ ፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ጽ/ቤት፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት የሰ/መ/ቁ 259947 ለዚህ የሰበር ክርክር ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን በከፍተኛዉ ፍርድ ቤት አመልካች ከሳሽ፣ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሾች በመሆን መከራከራቸዉን የሥር ፍ/ቤቶች ዉሳኔ ያመለክታል፡፡ ክርክሩ በማህበር በመደራጀት ከተገኘዉ ይዞታ ጋር የተያያዘ ሲሆን አመልካች በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተጠሪዎች ላይ ባቀረቡት ክስ በ03/08/1990 ዓ/ም ተመዝግቦ በፀደቀዉ የመተዳደሪያ ደንብ መሠረት የተደራጀ ታቦር የመኖሪያ ቤቶች ኅብረት ሥራ ማኅበር አባል በመሆን ተደራጅተዉ ማኅበሩ በሕጋዊ መንገድ ከመንግሥት ካገኘዉ ጠቅላላ ይዞታ ላይ መጠኑ 203.67 ካሬ ሜትር የሆነዉን የክርክሩን ይዞታ በድርሻ እንደሰጣቸዉና የዚሁ ይዞታ ሕጋዊ ባለመብት ስለመሆናቸዉም በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በመ/ቁጥር 281839 በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ኅብረት ሥራ ጽ/ቤትና በኮልፌ ቀራኒዮ ክለ ከተማ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት ላይ ክስ አቅርበዉ መብታቸዉ ተረጋግጦ ዉሳኔ እንዲያገኝ የሚል ነው፡መልካም ንባብ… Previous Article ወ/ሮ ሙርሽዳ ሁሴን እና ወ/ሮ አልፊያ ሁሴን (13) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 257243 Next Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594 Print 2512 Documents to download 259947(.pdf, 828.26 KB) - 417 download(s)
የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ላይ የሁለት ቀናት ስልጠና ተሰጠ የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ላይ የሁለት ቀናት ስልጠና ተሰጠ Monday, March 24, 2025 800 የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፌደራል የፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት እና ከኢትዮጵያ የማስማማትና ግልግል ዳኝነት ማዕከል (EMAC) ጋር በመተባበር የሁለት ቀናት ስልጠና ለፌደራል ከፍተኛ እና መጀመሪያ ፍርድ ቤት ረዳት ዳኞች ተሰጥቷል፡፡ Read more
ስዊድን አገር ለተደረገው የስራ ጉብኝትና ልምምድ ልውውጥ... ስዊድን አገር ለተደረገው የስራ ጉብኝትና ልምምድ ልውውጥ... Wednesday, March 19, 2025 843 የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከአውሮፓ ህብረት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እያከናወነ ከሚገኘው የወንጀል ፍትህ አስተዳደር መሻሻያ ተግባራት መካከል በወንጀል ፍትህ አስተዳደር የተሻለ ተሞክሮ ካላቸው አውሮፓ አገራት ፍርድ ቤቶች ልምድ መቅሰም ይገኝበታል። ይህንኑ ተከትሎ በቅርቡ 23 የፌደራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች ወደ ስዊድን አገር በመጓዝ ከአገሪቱ ፍ/ቤቶች ልምምድ መቅሰማቸው ይታወቃል፡: Read more
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት የአንድ... የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት የአንድ... Monday, March 17, 2025 734 የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት እና በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለሚ ኩራ ምድብ ችሎት በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል። Read more
የፍርድ ቤት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ መልካም ስነ ምግባርን... የፍርድ ቤት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ መልካም ስነ ምግባርን... Thursday, March 13, 2025 1015 በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መልካም ስነ-ምግባራዊ ባህርይ የተላበሰ አገልግሎት አሰጣጥን ለማጎልበት ስነልቦና፣ ስነምግባርና አገልግሎት አሰጣጥ በሚል ርዕስ መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከተቋሙ ልዩ ልዩ የስራ ክፍሎች ለተዉጣጡ 115 ሰራተኞች ተሰጥቷል፡፡ Read more
12Dec2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ የሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Friday, December 12, 2025 Read more
6Nov2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ ሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Thursday, November 6, 2025 Read more
8Oct2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ ሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Wednesday, October 8, 2025 Read more