Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ተስፋዬ ደገፋ እና ዶ/ር ትዕዛዙ ተፈራ ፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ጽ/ቤት፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት የሰ/መ/ቁ 259947

ለዚህ የሰበር ክርክር ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን በከፍተኛዉ ፍርድ ቤት አመልካች ከሳሽ፣ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሾች በመሆን መከራከራቸዉን የሥር ፍ/ቤቶች ዉሳኔ ያመለክታል፡፡ ክርክሩ በማህበር በመደራጀት ከተገኘዉ ይዞታ ጋር የተያያዘ ሲሆን አመልካች በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተጠሪዎች ላይ ባቀረቡት  ክስ በ03/08/1990 ዓ/ም ተመዝግቦ በፀደቀዉ የመተዳደሪያ ደንብ መሠረት የተደራጀ ታቦር የመኖሪያ ቤቶች ኅብረት ሥራ ማኅበር አባል በመሆን ተደራጅተዉ ማኅበሩ በሕጋዊ መንገድ ከመንግሥት ካገኘዉ ጠቅላላ ይዞታ ላይ መጠኑ 203.67 ካሬ ሜትር የሆነዉን የክርክሩን ይዞታ   በድርሻ እንደሰጣቸዉና የዚሁ ይዞታ ሕጋዊ ባለመብት ስለመሆናቸዉም በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በመ/ቁጥር 281839 በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ኅብረት ሥራ ጽ/ቤትና በኮልፌ  ቀራኒዮ ክለ ከተማ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት ላይ ክስ አቅርበዉ መብታቸዉ ተረጋግጦ ዉሳኔ እንዲያገኝ የሚል ነው፡መልካም ንባብ…

Previous Article ወ/ሮ ሙርሽዳ ሁሴን እና ወ/ሮ አልፊያ ሁሴን (13) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 257243
Next Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Print
2512

Documents to download

  • 259947(.pdf, 828.26 KB) - 417 download(s)

«December 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
24252627282930
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
2930311234

የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ላይ የሁለት ቀናት ስልጠና ተሰጠ

800

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፌደራል የፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት እና ከኢትዮጵያ የማስማማትና ግልግል ዳኝነት ማዕከል (EMAC) ጋር በመተባበር የሁለት ቀናት ስልጠና ለፌደራል ከፍተኛ እና መጀመሪያ ፍርድ ቤት ረዳት ዳኞች ተሰጥቷል፡፡

ስዊድን አገር ለተደረገው የስራ ጉብኝትና ልምምድ ልውውጥ...

843

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከአውሮፓ ህብረት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እያከናወነ ከሚገኘው የወንጀል ፍትህ አስተዳደር መሻሻያ ተግባራት መካከል በወንጀል ፍትህ አስተዳደር የተሻለ ተሞክሮ ካላቸው አውሮፓ አገራት ፍርድ ቤቶች ልምድ መቅሰም ይገኝበታል። ይህንኑ ተከትሎ በቅርቡ 23 የፌደራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች ወደ ስዊድን አገር በመጓዝ ከአገሪቱ ፍ/ቤቶች ልምምድ መቅሰማቸው ይታወቃል፡:

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት የአንድ...

734

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት እና በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለሚ ኩራ ምድብ ችሎት በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል።

የፍርድ ቤት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ መልካም ስነ ምግባርን...

1015

በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መልካም ስነ-ምግባራዊ ባህርይ የተላበሰ አገልግሎት አሰጣጥን ለማጎልበት ስነልቦና፣ ስነምግባርና አገልግሎት አሰጣጥ በሚል ርዕስ መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከተቋሙ ልዩ ልዩ የስራ ክፍሎች ለተዉጣጡ 115 ሰራተኞች ተሰጥቷል፡፡

First1314151618202122Last