Selam Warga / Tuesday, June 17, 2025 / Categories: CASSATION, Cassation አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395 ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594 Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230 Print 3072 Documents to download 266395(.pdf, 849.74 KB) - 542 download(s)
የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ላይ የሁለት ቀናት ስልጠና ተሰጠ የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ላይ የሁለት ቀናት ስልጠና ተሰጠ Monday, March 24, 2025 800 የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፌደራል የፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት እና ከኢትዮጵያ የማስማማትና ግልግል ዳኝነት ማዕከል (EMAC) ጋር በመተባበር የሁለት ቀናት ስልጠና ለፌደራል ከፍተኛ እና መጀመሪያ ፍርድ ቤት ረዳት ዳኞች ተሰጥቷል፡፡ Read more
ስዊድን አገር ለተደረገው የስራ ጉብኝትና ልምምድ ልውውጥ... ስዊድን አገር ለተደረገው የስራ ጉብኝትና ልምምድ ልውውጥ... Wednesday, March 19, 2025 842 የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከአውሮፓ ህብረት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እያከናወነ ከሚገኘው የወንጀል ፍትህ አስተዳደር መሻሻያ ተግባራት መካከል በወንጀል ፍትህ አስተዳደር የተሻለ ተሞክሮ ካላቸው አውሮፓ አገራት ፍርድ ቤቶች ልምድ መቅሰም ይገኝበታል። ይህንኑ ተከትሎ በቅርቡ 23 የፌደራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች ወደ ስዊድን አገር በመጓዝ ከአገሪቱ ፍ/ቤቶች ልምምድ መቅሰማቸው ይታወቃል፡: Read more
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት የአንድ... የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት የአንድ... Monday, March 17, 2025 734 የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት እና በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለሚ ኩራ ምድብ ችሎት በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል። Read more
የፍርድ ቤት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ መልካም ስነ ምግባርን... የፍርድ ቤት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ መልካም ስነ ምግባርን... Thursday, March 13, 2025 1015 በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መልካም ስነ-ምግባራዊ ባህርይ የተላበሰ አገልግሎት አሰጣጥን ለማጎልበት ስነልቦና፣ ስነምግባርና አገልግሎት አሰጣጥ በሚል ርዕስ መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከተቋሙ ልዩ ልዩ የስራ ክፍሎች ለተዉጣጡ 115 ሰራተኞች ተሰጥቷል፡፡ Read more
12Dec2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ የሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Friday, December 12, 2025 Read more
6Nov2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ ሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Thursday, November 6, 2025 Read more
8Oct2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ ሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Wednesday, October 8, 2025 Read more