Selam Warga / Tuesday, June 17, 2025 / Categories: CASSATION, Cassation አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395 ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594 Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230 Print 3072 Documents to download 266395(.pdf, 849.74 KB) - 542 download(s)
የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ማሻሻያ ረቂቅ ላይ... የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ማሻሻያ ረቂቅ ላይ... Monday, March 10, 2025 771 ላለፉት አስራ አንድ ዓመታት በሥራ ላይ የቆየውን የፍርድ ቤቶች የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ለማሻሻል ተዘጋጅቶ በቀረበ ረቂቅ መመሪያ ላይ ግብአት ለማሰባሰብ የተዘጋጀና የፌደራል ፍርድ ቤቶችን ጨምሮ ከሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ጥሪ የተደረገላቸው 160 ያህል ዳኞች፣ ዐቃቢያነ ሕግ፣ ጠበቆች እና ሌሎች የሕግ ባለሙያዎች የተሳተፉበት የምክክር መድረክ የካቲት 29 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሔደ፡፡ Read more
በከባድና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ላይ የተዘጋጀ ሥልጠና... በከባድና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ላይ የተዘጋጀ ሥልጠና... Monday, March 3, 2025 864 ለፌደራል ፍርድ ቤቶች እና ከሁሉም ክልል ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ ዳኞች እንዲሁም ለወታደራዊ ፍርድ ቤት ዳኞች በከባድና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ላይ የተዘጋጀ የአንድ ቀን ስልጠና የካቲት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሄደ፡፡ Read more
የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የለውጥ ሥራ ተፈጻሚ ለማድረግ... የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የለውጥ ሥራ ተፈጻሚ ለማድረግ... Thursday, February 27, 2025 768 በፌደራል ፍርድ ቤቶች የተጀመረውን የለውጥ ሥራ ተፈጻሚ ለማድረግ የፍርድ ቤቶችን የሰው ኃይል አቅም መገንባት ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ መሆኑን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ አበባ እምቢአለ ገለጹ፡፡ Read more
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ልዑክ ቡድን በፌዴራል... የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ልዑክ ቡድን በፌዴራል... Wednesday, February 26, 2025 762 የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ሚኒስትር ዴኤታዎች እንዲሁም ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችን ያካተተ የልዑክ ቡድን በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በቀን 18/06/2017 ዓ.ም በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል፡፡ Read more
12Dec2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ የሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Friday, December 12, 2025 Read more
6Nov2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ ሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Thursday, November 6, 2025 Read more
8Oct2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ ሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Wednesday, October 8, 2025 Read more