Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
3072

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 542 download(s)

«December 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
24252627282930
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
2930311234

የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ማሻሻያ ረቂቅ ላይ...

771

ላለፉት አስራ አንድ ዓመታት በሥራ ላይ የቆየውን የፍርድ ቤቶች የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ለማሻሻል ተዘጋጅቶ በቀረበ ረቂቅ መመሪያ ላይ ግብአት ለማሰባሰብ የተዘጋጀና የፌደራል ፍርድ ቤቶችን ጨምሮ ከሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ጥሪ የተደረገላቸው 160 ያህል ዳኞች፣ ዐቃቢያነ ሕግ፣ ጠበቆች እና ሌሎች የሕግ ባለሙያዎች የተሳተፉበት የምክክር መድረክ የካቲት 29 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሔደ፡፡

በከባድና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ላይ የተዘጋጀ ሥልጠና...

864

ለፌደራል ፍርድ ቤቶች እና ከሁሉም ክልል ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ ዳኞች እንዲሁም ለወታደራዊ ፍርድ ቤት ዳኞች በከባድና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ላይ የተዘጋጀ የአንድ ቀን ስልጠና የካቲት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሄደ፡፡

የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የለውጥ ሥራ ተፈጻሚ ለማድረግ...

768

በፌደራል ፍርድ ቤቶች የተጀመረውን የለውጥ ሥራ ተፈጻሚ ለማድረግ የፍርድ ቤቶችን የሰው ኃይል አቅም መገንባት ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ መሆኑን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ አበባ እምቢአለ ገለጹ፡፡

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ልዑክ ቡድን በፌዴራል...

762

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ሚኒስትር ዴኤታዎች እንዲሁም ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችን ያካተተ የልዑክ ቡድን በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በቀን 18/06/2017 ዓ.ም በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል፡፡

First1415161719212223Last