Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

ሐረማያ ዩንቨርስቲ እና መላ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግል ማሕበር የሰ/መ/ቁ. 253530

ጉዳዩ ከግንባታ ውል ጋር በተያያዘ በስር ፍ/ቤት የተሰጠው ውሳኔ በቀረበው የዳኝነት ጥያቄ መሰረት መሆን አለመሆኑን የሚመለከት ነው፡፡ የሰበርአቤቱታው የቀረበው የፌደራል ጠቅላይፍርድ ቤት በሠጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል ነው፡፡ የክርክሩን አመጣጥ ከስር ፍርድ ቤት የመዝገብ ግልባጭ እንደተረዳነው በሥር ፍርድ ቤት አመልካች ከሳሽ ሲሆን ተጠሪ ተከሳሽ ነበር፡፡አመልካች በ20/01/2013 ዓ/ም ጽፎ ባቀረበው ክስ አመልካች እና ተጠሪ በነሀሴ 2009ዓ/ም እ.ኤ.አ የማስፋፊያ ግንባታ ለማከናወን ተስማምተው ተጠሪ ሳይቱን በመረከብ የግንባታ ማስፋፊያ ስራውን ጀምሮ የነበረ ቢሆንም በውሉ በተቀመጠው ጊዜ እና ጥራት የግንባታ ስራውን ማከናወን ባለመቻሉ በተደጋጋሚ ማስጠንቀቅያ ሰጥቶ ስራው 93% ላይ እያለ አመልካች ውሉን አቋርጧል፡፡ በመሆኑም ለአምስት ሕንፃዎች/ብሎኮች የስራ ግድፈት ማስተካከያ ብር 2,031,357.91፣ ለኩሽና፣ መጽሀፍት ቤትና ምግብ ቤት ማስተካከያ ሥራ ብር 350,759.30፣ የውሉ አፈጻጸም በመዝግየቱ በውሉ አንቀጽ 49.1 መሰረት የጠቅላላ ውሉን ዋጋ 10% የደረሰ ኪሣራ ብር 5,219,807.91እና የቀሪ ሥራ ማጠናቀቂያ ብር 492,255.18በድምሩ ብር 10,107,964.5 ተጠሪ እንዲከፍል እንዲወሰንለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡መልካም ንባብ…..

Previous Article አቶ ቴዎድሮስ መስፋን ህንፃ ሥራ ተቋራጭእና አዲስ አበባ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት (በአሁኑ - የአ/አ ቤ/ልማት ኮርፖሬሽን) የሰበር መ/ቁ 253303
Next Article ወ/ሮ ኢየሩሳሌም ኃይሉ እና እነ ወ/ሮ እታገኘው ኃይሉ(4ሰዎች) የሰ/መ/ቁጥር 253718
Print
4629

Documents to download

  • 253530(.pdf, 849.38 KB) - 631 download(s)

«June 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
25262728293031
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
293012345

‎በመሰረታዊ የክስ መደራደር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ...

44

ከፌዴራልና ከክልል ለተውጣጡ የዳኝነትና የፍትህ አካላት አመራሮች፣ ዳኞች እንዲሁም የሕግ ባለሙያዎች በመሰረታዊ የክስ መደራደር ( Plea bargaining) ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከፔፐርዳይን ዩኒቨርሲቲ በተጋበዙ አሰልጣኞች ተሰጥቷል።

የኬንያ ፍርድ ቤት ልኡክ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት...

169

የኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ እና የጄሲኢ (JCE) ሰብሳቢ በሆኑት ክብርት ዳኛ ሱዛን ኞኪ ንዱንጉ የተመራው የልዑካን ቡድን፣ በኢትዮጵያ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት በክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን የልምድ ልውውጥ ውይይቶችን እያደረገ ይገኛል።

የዓለም አቀፍ የሰብአዊነት ሕግ ምስለ ችሎት ውድድር ተካሄደ

294

የ9ነኛው አገር አቀፍ የዓለም አቀፍ የሰብአዊነት ሕግ ምስለ ችሎት (IHL Moot Court) ውድድር የአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጋር በመተባበር በጦርነት ቀውስ ወቅት የሕፃናትና ትምህርት ጥበቃ በሚል ጭብጥ ተካሂዷል፡:

 

245678910Last