Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
7349

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 971 download(s)

«July 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
293012345
6789101112
13141516171819
20212223242526
272829303112
3456789

የፍርድ ቤቶች ዲጅታላይዜሽን እና አዲሱን መመሪያ...

1767

ፌዴራል ፍ/ቤቶችን በራሳቸዉ ኔትወርክ የማስተሳሰር እና አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ለማድረግ መሰረት ይሆን ዘንድ ላለፉት ዓመታት ፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት እያስገነባ የነበረዉ ክላዉድ የመረጃ ቋት ያለዉ እና ደህንነቱ የተረጋገጠ የዋይድ ኤሪያ ኔትወርክ መሰረተ ልማት ዝርጋታ እየተጠናቀቀ ይገኛል።

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ኘሬዝዳንት ክቡር አቶ...

1681

በጉብኝታቸውም የ2017 ዓ.ም በሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በክልሉ ፍርድ ቤቶች የተጀመሩ የለውጥ ስራዎችን በተመለከተ በሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ደምሴ ዱላቻ ገለፃ ተደርጎላቸዋል፡፡

ዓመታዊ የስራ ዕቅድና አፈጻጸም እንዲሁም የሰራተኞች...

2157

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ዘርፍ ሠራተኞች የተሳተፉበትና በፍርድ ቤቱ የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም እና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ የሀሳብ ልውውጥ የተደረገበት የውይይት መድረክ ነሐሴ 24 እና 25 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሔደ፡፡

የፌደራል ፍርድ ቤቶች የፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት የአሰራር...

1687

የፌደራል ፍርድ ቤቶች የፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት የአሰራር ስርዓት መመሪያ ላይ የቫሊዴሽን ወርክሾፕ በቀን 24/12/2017 ዓ.ም የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝደንት፣ የጀስቲስ ፎር ኦል ፕሪዝን ፌሎሺፕ ኢትዮጵያ ምክትል ፕሬዝደንት፣ የፌደራል ፍርድ ቤት ዳኞች እና የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡

First1617181921232425Last