Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ተገኝ ደምሴ ወንድአፍራሽ እና ወ/ሮ አየለች ደሳለኝ እንዳሻው የሰበር መ/ቁጥር 248810

ጉዳዩ የንብረት መፋለም ክስን የሚመለከት ነው፡፡ የሰበር አቤቱታው የቀረበው የሐረሪ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመ/ቁ.13375 በቀን 18/11/2011 ዓ/ም የሰጠውን ውሳኔ የክልሉ  ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ችሎት በመ/ቁ. 04927 በቀን 01/04/2012 ዓ/ም የቀረበውን ይግባኝ ቅሬታ ባለመቀበል የሥር ፍርድ ቤትን ውሳኔ በትዕዛዝ በማጽናት የሰጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል አመልካች ሰኔ 09 ቀን 2015ዓ/ም በተጻፈ አቤቱታ ቅሬታ በማቅረባቸው ነው፡፡

 ከሥር ፍርድ ቤቶች የመዝገብ ግልባጭ እንደተረዳነው በሥር ፍርድ ቤት አመልካች ተከሳሽ  ተጠሪ ከሳሽ ሆነው ተከራክረዋል፡፡ ተጠሪ በ23/03/2008ዓ/ም ጽፈው ባቀረቡት ክስ አዋሳኞቹ በክሱ የተጠቀሰው የቤት ቁጥር 144 የሆነ በ 2921 ካ.ሜ የመሬት ይዞታ ላይ ያረፈ ሰባት ክፍሎች ያሉት ፎቅ ቤትና ሰርቪስ ቤት ሟች እህታችን በግዥ አግኝተው ሲጠቀሙበት ቆይተው በ1962 ዓ/ም በነበረው የሶማሊያ ጦርነት ወጥተው ስላልተመለሱ ተጠሪ ከወንድሜ ሻምቤል ፈለቀ ደሳለኝ ጋር በመሆን የእህታችንን መጥፋት እና ወራሽነት በ1972 ዓ/ም አሳውጀውን ቤቱ በውርስ ለተጠሪ እና ወንድሜ ከተላለፈ በኃላ፤ የተጠሪ ወንድም በ1988 ዓ/ም በውርስ ያገኙትን የአከራካሪውን ቤት ድርሻ በስጦታ ያስተላለፉልኝን ጨምሮ ከጠቅላላ ይዞታ ውስጥ በ1394 ካ/ሜ ላይ ካርታ በስሜ 11/09/1996 ዓ/ም የተሰራልኝ ሲሆን ቀሪው 1527 ካ/ሜ ይዞታ እና ፎቅ ቤት ወደ ፊት ይሰራልሻል ተብዬ ነበር፤ከዚያ በኋላ ሟች እህቴ ያከራየቻቸው የተከሳሽ ቤተሰቦችከ1969 ዓ/ም ጀምሮ በቤት ውስጥ መኖር ቀጠሉ፤ አመልካች ምንም መብት ሳይኖረው በምዕራብ አቅጣጫ የሚገኙትን አምስት ክፍል ቤቶችን ይዞ በማከራየት፤ ከ2001 ዓ/ም እስከ 2004 ዓ/ም ተለጣፊ ቤቶችን በመስራት እየተጠቀሙ በመሆኑና ቤቱንም ለማስረከብ ፈቃደኛ ስላልሆኑ በሕገ-ወጥ መንገድ የሠሩትን ቤት አፍርሰው የቤት ቁጥር 144 እና ይዞታውን ለቀው እንዲያስረክቡ ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ…

Previous Article ቁአቶ ጌታቸው ጎነሞ እና አቶ ፍሰሀ ታምራትየሰ/መ/ቁ249348
Next Article የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ገቢዎች ቢሮ ዓቃቤ ሀግ እና ወ/ሮ መዓዛ በልስቲየሠ/መ/ቁጥር 248735
Print
4542

Documents to download

  • 248810(.pdf, 854.77 KB) - 579 download(s)

«June 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
25262728293031
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
293012345

በምርጫ ነክ ጉዳዮች ላይ ለዳኞች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና...

220

‎የዳኝነትና የፍትህ አካላት በምርጫ ሂደት ወቅት የሰብአዊ መብት ጥበቃን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ዓለም አቀፍ የህግ ማዕቀፎች እና ተሞክሮዎች ላይ በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን እና በተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጽሕፈት ቤት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል።

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈፃፀም ...

280

በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የ2018 በጀት አመት የ9 ወራት የስራ አፈፃፀም ሪፖርትን አዳምጦ በተሰሩት ስራዎች ላይ በርካታ ነገሮች መሻሻላቸውን ገልፆ በቀጣይ መታረም አለባቸው ያላቸው ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ አስቀምጧል።

የዳኝነት ስርዓትን ለማዘመን እየተሰራ ያለው ስራ የሚደነቅ...

263

በኢትዮጵያ የቤልጂየም አምባሳደር እና የአፍሪካ ሕብረት ቋሚ ተወካይ ክብርት ዶ/ር አኔሊስ ቨርስቲሸል በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተገኝተው በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

በኢትዮጵያ የአዘርባጃን አምባሳደር ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ...

258

በኢትዮጵያ የአዘርባጃን አምባሳደር እና የአፍሪካ አንድነት ቋሚ ተወካይ የተከበሩ ሩስላን ናሲቦቭ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተገኝተው በጋራ መስራት በሚቻል በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡

135678910Last