Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ሰለሞን አርአያ እናእነ ህፃን ዳንኤል ቴውድሮስ ሞግዚት ወ/ሮ የሺ መንግስቱ(5ሰዎች)የሰ/መ/ቁጥር፡- 255592

ጉዳዩ የውርስ ማጣራትን የሚመለከት ሆኖ አቤቱታው በቀረበበት የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት አመልካች 5ኛ ጣልቃ ገብ ፣ 2ኛ ተጠሪ የስር ተጠሪ፤1ኛ ተጠሪ የስር አመልካች፤  ከ3ኛ እስከ 5ኛ ያሉ ተጠሪዎች ደግሞ 3ኛ፤4ኛ እና 6ኛ ጣ/ገቦች ነበሩ፡፡ የክርክሩ አመጣጥ በአጭሩ፡- የአሁን 1ኛ ተጠሪ  ባቀረቡት አቤቱታ የሟች ባለቤታቸው ቴውድሮስ አርአያ ወላጆች የልጃቸው አያት የሆኑት ጀነራል አርአያ ዘርዓይ ጥር 25 ቀን 2003 ዓም እናቱ ወ/ሮ ሰነዳይ ሀይሌ ጥር 04 ቀን 2004 ዓም ከዚህ አለም በሞት የተለዩ መሆኑን፤ባለቤታቸው ከወንድሞቹና እህቶቹ ጋር በመሆን በ29/08/2005 ዓም ወራሽነታቸውን ያረጋገጡ ቢሆንም ውርሱ ሳይጣራ መኖሪያ ቤቱን ሳይከፋፈሉ በጋራ ይዘው ሲጠቀሙበት ቆይተው ከ2006 ዓም ጀምሮ ቤቱን አከራይተው የኪራዩን ገንዘብ እኩል እየተካፈሉ መሆኑን ገልጠው ድርሻቸውን ለይተው ለማወቅና ለማረጋገጥ እንዲችሉ የውርስ ሀብት እንዲጣራ ጠይቀዋል፡፡ መልካም ንባብ…..

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ጫላእና አቶ ሸዋንግዛው ሽብሩ/ቁጥር የሰ/መ/ቁ 254862
Next Article አቶ ዮሀንስ ካሳዬ እና የፍትህ ሚኒስቴር ዓቃቤ ሕግ የሠ/መ/ቁጥር 273594
Print
4649

Documents to download

  • 255592(.pdf, 834.83 KB) - 666 download(s)

«May 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
27282930123
45678910
11121314151617
18192021222324
25262728293031
1234567

ሀገር አቀፍ የዳኝነት እና የፍትህ አካላት የጋራ መድረክ...

209

ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው አመታዊ ሀገር አቀፍ የዳኝነት እና የፍትህ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ (ጆይንድ አፕ ጀስቲስ ፎረም) የፌዴራልና የክልል የዳኝነትና የፍትህ አካላት የጋራ መድረክ የመግባቢያ ሰነድ የፊርማ ስነ ስርዓት በማከናወን ተጠናቋል።

የዳኝነትና የፍትህ አካላት በጋራ የሚመክሩበት፣...

180

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በመክፈቻ ንግግራቸው፤ የሕግ የበላይነት የተረጋገጠባት እና ፍትሕ የሰፈነባት ሀገር ከመገንባት አንጻር በጋራ ስራዎች ላይ ለመምከርና የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ የመድረኩ ሚና ከፍተኛ እንደሆነ በማንሳት፤ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በጋራ በመፍታት ተቋማዊም ሆነ የወል ግቦችን ማሳካት እንደሚቻል ገልጸዋል።

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ሰሚ ችሎት የወንጀል...

280

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከአውሮፓ ህብረት ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ሁለት የስልጠና ማኑዋሎች ማለትም ተከታታይ የወንጀል ችሎት አመራር ሥልጠና ማንዋል( Training Manual on continuous criminal trials )፣ ድንበር ተሻጋሪ እና ከባድ ወንጀሎች ሥልጠና ሞጁል(Training Module on Trans-Boundary and grave crimes) እንዲሁም "በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ሰሚ ችሎት የወንጀል ህግ ትርጉም ውሳኔዎች ስብስብ በጉዳዮች የተደራጁ ልዩ ዕትም" መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ.ም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የማስተዋወቅ ፕሮግራም አካሂዷል ፡፡

በፍትህ ስርአቱ ውስጥ ለሚያገለግሉ የሶሻል ወርክ...

278

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የተባባሩት መንግስታት የህዝብ ፈንድ(UNFPA) የጋራ ትብብር በፍትህ ስርአት ውስጥ የሚገለግሉ የሶሻል ወርክ ባለሞያዎችን እውቀት እና ከህሎት በተሻለ ለመገንባት እየተዘጋጀ የሚገኘው የስልጠና ማኑዋል ረቂቅ ላይ የውይይት እና ግብአት ማሰባሰቢያ መድረክ በቀን 12/7/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡

135678910Last