Selam Warga / Tuesday, June 17, 2025 / Categories: CASSATION, Cassation አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395 ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594 Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230 Print 7392 Documents to download 266395(.pdf, 849.74 KB) - 972 download(s)
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ስራ ሃላፊዎች የፕሮጀክት... የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ስራ ሃላፊዎች የፕሮጀክት... Wednesday, March 20, 2024 4080 የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የፍትሕ ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎች ከአውሮፓ ህብረት የወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ማሻሻያ ፕሮጀክት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ የፕሮጀክት አስተዳደር የ5 ቀን ስልጠና ወስደዋል፡፡ Read more
በህፃናት የቀለብ አወሳሰን ረቂቅ መመሪያ ላይ ዉይይት ተደረገ በህፃናት የቀለብ አወሳሰን ረቂቅ መመሪያ ላይ ዉይይት ተደረገ Wednesday, March 13, 2024 2881 የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህፃናት ፍትህ ፕሮጀክት ፅ/ቤት ባዘጋጀዉ የህፃናት ቀለብ አወሳሰን ረቂቅ መመሪያ ላይ የግብአት ማሰባሰብያ ዉይይት አድርጓል፡፡ Read more
ዜና ሹመት ዜና ሹመት Tuesday, March 12, 2024 5258 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 16ኛ መደበኛ ስብሰባ የ16 የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞችን ሹመት አጸደቀ Read more
የካናዳ ፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና ጠቅላይ አቃቤ ህግ... የካናዳ ፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና ጠቅላይ አቃቤ ህግ... Tuesday, March 12, 2024 2580 የካናዳ ፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና ጠቅላይ አቃቤ ህግ ክቡር አቶ አሪፍ ቪራኒ ከልዑክ ቡድናቸው ጋር በመሆን በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል፡፡ Read more
10Mar2026 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ የሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Tuesday, March 10, 2026 Read more