Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
7489

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 976 download(s)

«July 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
293012345
6789101112
13141516171819
20212223242526
272829303112
3456789

የካናዳ ፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና ጠቅላይ አቃቤ ህግ...

2633

የካናዳ ፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና ጠቅላይ አቃቤ ህግ ክቡር አቶ አሪፍ ቪራኒ ከልዑክ ቡድናቸው ጋር በመሆን በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል፡፡

ለፍርድ ቤት ዘርፍ አመራሮች በሥነ-ምግባር መርሆዎች ላይ...

2876

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር ከሶስቱም የፌደራል ፍርድ ቤቶ ለተውጣጡ የፍርድ ቤት ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ከየካቲት 28-29 ቀን 2016 ዓ.ም በፍርድ ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ 

በፍርድ ቤቱ አዲስ የህንፃ ግንባታ ዲዛይን ስራ ላይ ...

2804

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፍተኛ አመራሮች፤፡ የዳኞች ተወካዮች እና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸዉ የስራ ሃላፊዎች የካቲት 27 ቀን 2016 ዓ.ም አዲስ ሊያስገነባ ባቀደዉ የህንፃ ዲዛይን ስራ ላይ ተወያይተዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር...

7734

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከኢትዮጵያ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር የፍርድ ቤትን አሰራር ይበልጥ ለማዘመን የካቲት 27 ቀን 2016 ዓ/ም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቅጥር ግቢ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ የስምምነቱ አላማ ተቋማቱ ከኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ እና ተያያዥ ፕሮጀክቶች ጋር በተገናኘ ዘላቂነት ያለው ትብብርና ስኬታማ የአሰራር ዘዴዎችን እንዲፈጥሩ ለማስቻል ነው።

First4647484951535455Last