የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የ2016 ዓ.ም የስድስት ወር አፈጻጸም ግምገማና ውይይት በቀን 09/06/2016 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ በአፈጻጸም ግምገማው የዳኞች እና አስተዳደር ሰራተኞች የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማና ውይይት የተደረገ ሲሆን ከዚህ ጋር ተያይዞ የጉዳዮች ፍሰት አፈጻጸም ሪፖርት፣ የኢንስፔክሽን ግኝት ሪፖርት፣ የፌደራል ፍርድ ቤቶች አይ.ሲ.ቲ ፕሮጀክቶች የተመለከተ ገለጻ እንዲሁም የህጻናት ተስማሚ ፍ/ቤቶች ረቂቅ መመሪያ ላይ ገለጻና ውይይት ተደርጓል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ የአስተዳደር ሰራተኞች አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ላይ ከየስራ ክፍሎቹ የአፈጻጸም ግምገማና ውይይት በተጨማሪ የአስተዳደር ሰራተኞች ደንብ 01/2015 ላይ ገለጻ ተደርጓል፡፡