Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
7489

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 976 download(s)

«July 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
293012345
6789101112
13141516171819
20212223242526
272829303112
3456789

የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍ/ቤት እና...

2549

የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍ/ቤት እና የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ልዑክ ቡድን በቀን 02/05/2016 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት በመገኘት የልምድ ልውውጥ እና ጉብኝት አድርገዋል፡፡ በጉብኝቱ ወቅት ከ ፌደራል ፍርድ ቤቶች የስራ ሀላፊዎች ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን የፌደራል ፍርድ ቤቶች አስተዳደር ሰራተኞች ደንብ፣ የመዋቅር ዝግጅትና የፌደራል ፍርድ ቤቶች የአይ.ሲ.ቲ (ኢንፎርሜሽንና ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ) ፕሮጀክቶች በሚመለከት ላይ ሰፊ ገለጻ ተደርጓል፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት በሀረሪ ክልል...

6930

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በሀረሪ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን የሁለቱ ተቋማት ፕሬዚደንቶች በየተቋሞቻቸው የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን ለማሳካት በጋራ መስራት በሚቻልበት ሁኔታዎች ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ በስራ ጉብኝቱ ወቅት በሀረሪ ክልል ፍርድ ቤቶች እየተከናወኑ ስለሚገኙ የሪፎርም ተግባራትን በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት በክቡር አቶ ማሂር አ/ሰመድ ገለፃ ተደርጓል።

ፍ/ቤቱ ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት...

2517

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ያለማቸውን አውቶማቲክ ትራንስክሪፕሽን፣ ስማርት ቻትቦት እና ዲጂታል የመረጃ ዴስክ የያዘ የስማርት ኮርት ሩም ሲስተም በታህሳስ 27 ቀን 2016 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ እንዲሁም ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በይፋ ተመርቋል፡፡

በፌደራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጡን...

2208

ክቡር ፕሬዚደንቱ ይህን የገለጹት ከታህሳስ 24-25 ቀን 2016 ዓ.ም በሐረሪ ክልላዊ መንግሥት አስተናጋጅነት በሐረር ከተማ በተካሄደው አራተኛው አገር አቀፍ የሕግ አውጭዎች የጋራ ምክክር መድረክ ላይ ነው፡፡

First4849505153555657Last