Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
6470

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 889 download(s)

«June 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
25262728293031
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
293012345

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከወርልድ ባንክ ስታር...

1940

የስልጠናው አላማ ዳኞችን በህገወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሙስና ወንጀሎች ሀብት ማስመለስ እና ሌሎች ተያያዥ የወንጀል ጉዳዬች እና የፍርድ ሂደቶች ላይ በአለም አቀፍ ተሞክሮዎች ላይ ግንዛቤ ለማስጨበጥ እና በጉዳዩ ዙሪያ የኢትዬጵያ ህግ ምን ይላል የሚለውን በተመለከተ ውይይት ለማድረግ ሲሆን ስልጠናው ከህዳር 7 እስከ ህዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል፡፡

በፍርድ ቤት በማስረጃነት ሲቀርቡ ቴምብር ቀረጥ...

2871

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ገቢዎች ቢሮ በፍርድ ቤት በማስረጃነት በሚቀርቡ ሠነዶች ላይ የቴምብር ቀረጥ ለማስለጠፍ እና ቀረጥ በተመን ለማስከፈል ባለጉዳዮች ክርክራቸውን በሚያቀርቡበት ምድብ ችሎቶች አቅራቢያ አገልግሎቱን ለመስጠት ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም የመግባቢያ ስምምነት የተፈራረሙ መሆኑ ይታወቃል፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የዳኝነት ስርዓት የውጭ አማካሪ...

2956

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በአዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 53 መሰረት ከቀድሞ ዳኞች፣ ከፍተኛ ልምድ እና ብቃት ካላቸው የህግ ባለሙያዎች እና ከዩኒቨርሲቲ ምሁራን ከተውጣጡ አካላት የአማካሪ ምክር ቤት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ አበባ እምቢአለ በተገኙበት ጥቅምት 19 ቀን 2016 ዓ.ም አቋቋመ፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የአዲስ አበባ ከተማ...

2369

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ገቢዎች ቢሮ በፍርድ ቤቶች በማስረጃነት በሚቀርቡ ሠነዶች ላይ የቴምብር ቀረጥ ለማስለጠፍ እና ቀረጥ በተመን ለማስከፈል ባለጉዳዮች ክርክራቸውን በሚያቀርቡበት ምድብ ችሎቶች አቅራቢያ አገልግሎቱን ለመስጠት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

First5152535456585960Last