ከፌደራል ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ ዳኞች እና የሥራ ኃላፊዎች በአመራር ክህሎት (Leadership) ላይ የተዘጋጀ ሥልጠና በአሜሪካ አገር ከሚገኘውና ችክፍሌ (Chick-fil-A) ከተሰኘው ድርጅት በመጡ ስድስት ባለሙያዎች ሰኔ 19 ቀን 2015 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል ተሰጠ፡፡
ሥልጠናው የመሪነት ጽንሰ-ሐሳብ እና የጥሩ መሪ ስብዕናዎች የተዳሰሱበት ሲሆን በኃላፊነት ላይ የተቀመጡና በሥራቸው ውጤታማ የሆኑ ግለሰቦች ሁሉ መሪ (Leader) ሊሆኑ እንደማይችሉም ተገልጿል፡፡