Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
4825

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 720 download(s)

«March 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
2324252627281
2345678
9101112131415
16171819202122
23242526272829
303112345

ለቋሚ ኮሚቴ አባላት በፌደራል ፍርድ ቤቶች አስተደደር...

1901
በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚፀድቅ በሚጠበቀው የፌደራል ፍርድ ቤቶች አስተዳደር ሠራተኞች ረቂቅ ደንብ ይዘት ላይ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ለሕግና ፍትሕ ቋሚ ኮሚቴ እና ለሰው ሐብት ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች እና አባላት መጋቢት 2 ቀን 2015 ዓ.ም ገለጻ ተደረገ፡፡

በፌደራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ነጻነት፣ ተጠያቂነትና...

1965
በፌደራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ነጻነት፣ ተጠያቂነትና የሕግ ማዕቀፎች ዙሪያ ከሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሕግና ፍትሕ ቋሚ ኮሚቴ እና ከሰው ሐብት ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ጋር መጋቢት 1 ቀን 2015 ዓ.ም የምክክር መድረክ ተካሔደ፡፡

በፌደራል ፍርድ ቤቶች የሴቶችን ተሳትፎና እኩልነት...

1682

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት በፌደራል ፍርድ ቤቶች የሴቶችን ተሳትፎና እኩልነት ለማረጋገጥ የሚረዱ የተለያዩ የፖሊሲ እርምጃዎችን እየወሰደ እንደሚገኝ የፍ/ቤቱ ም/ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ አበባ እምቢአለ ገለጹ፡፡

First5455565759616263Last