Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ኃይለ ጊዮርግስ ይልማ ወልደአብ እና እነ አቶ አዲስ እሸቱ (4) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 252056

ለዚህ የሰበር አቤቱታ ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን በወረዳዉ ፍርድ ቤት 1ኛ ተጠሪ ከሳሽ የአመልካች አዉራሽ ሟች አቶ ይልማ ወልደአብና ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ 1ኛ ተጠሪ በጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተራ ቁጥር ላይ በተጠቀሱት ተጠሪዎችና በአመልካች አባት በሟች አቶ ይልማ ወልደአብ ላይ ባቀረቡት ክስ በክሱ ላይ አዋሳኞቹ የተመለከተዉን 400 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈዉን  የመኖሪያ ቤት ከነሰርቪስ  ቤቶቹ ጭምር የካቲት 27 ቀን 2011 ዓ/ም በተፈረመ የሽያጭ ዉል ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (ከሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) በብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ) ገዝተዉ ካርታ በስማቸዉ የተሰጣቸዉ ቢሆንም በይዞታዉ ላይ ካሉ ቤቶች መካከል አንዱን የአመልካች ወላጅ አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) ይዘዉ ለመልቀቅ ፈቃደኛ አለመሆናቸዉን ገልፀዉ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (የሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) የሸጡላቸዉን ቤት ከአመልካች አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) አስለቅቀዉ እንዲያስረክቡና የአመልካች አባትም (የሥር 4ኛ ተከሳሽም) መብት ሳይኖራቸዉ የያዙትን የ1ኛ ተጠሪን (የሥር ከሳሽን) ቤት ለቀዉ እንዲወጡ እንዲወሰንላቸዉ ዳኝነት በመጠየቅ ክስ አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ….

Previous Article የፌደራል ዐቃቤ ህግ እና አቶ አበበ ወንድሙ ኤጋ የሰ/መ/ቁጥር 251759
Next Article የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አቶ መጣልኝ መላኩ የሰ.መ.ቁ.252953
Print
2670

Documents to download

  • 252056(.pdf, 838.15 KB) - 341 download(s)

«January 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
2930311234
567891011
12131415161718
19202122232425
2627282930311
2345678

የአፍሪካ ህገ መንግስታዊ ፍርድ ቤቶችና ጠቅላይ ፍርድ ቤት...

285

4ኛውን የአፍሪካ ህገመንግሥታዊ ፍርድ ቤቶች እና መሰል ተቋማት ዓለም አቀፍ ሲምፖዝየም ‘ህገ መንግሥታዊነት እና ሀገረ መንግሥት ግንባታ’ በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ መካሄዱን ተከትሎ የመርሃግብሩ ተሳታፊ እንግዶች በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በቀን 20/03/2018 ዓ.ም በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል።

ለፌደራል ፍርድ ቤቶች የቤተሰብ ችሎት ዳኞች የልምድ...

406

የኢንግላንድ እና ዌልስ ጠበቆች ማህበር ፕሬዚዳንት የሆኑት ክብርት ባርባራ ሚልስ በቀን 19/03/2018 ዓ.ም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ለፌደራል ፍርደ ቤቶች የቤተሰብ ችሎት ዳኞች ልምዳቸውን አካፈሉ፡፡

የላይቤሪያ ህገ መንግስታዊ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንትና ልዑክ...

335

የላይቤሪያ ህገ መንግስታዊ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ጄሚ ኩዊኪ (Honorable Jamie Quiqui Gbeisay) እና ልዑክ ቡድናቸው በቀን 17/03/2018 ዓ.ም የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት እና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጉብኝት አድርገዋል፡፡

በዲጂታል የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ በዋነኝነትም ...

384

በስልጠናው የማጠቃለያ ንግግር ያደረጉት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ ድሪባ ፈዬራ ክቡራን ዳኞች ላደረጉት ንቁ ተሳትፎና በመድረኩ ለተነሱት ገንቢ ሀሳብ አስተያየቶች አመስግነው ቴክኖሎጂው በቅርቡ ወደ ትግበራ ስለሚገባ ለትግበራው ውጤታማነት ስልጠናው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

123468910Last