Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
6109

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 857 download(s)

«May 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
27282930123
45678910
11121314151617
18192021222324
25262728293031
1234567

በፍርድ ቤቱ የተጀመረውን የማሻሻያ ሥራ ሊሸከም የሚችልና...

3040
በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዳኝነት አገልግሎት ዘርፍ እና በአስተዳደር ሥራዎች ዘርፍ የተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎችን ሊሸከም የሚችልና የሥነምግባር መርሆዎችን በአግባቡ የተገነዘበ፣ በሥነምግባር እሴቶች እየተመራ ኃላፊነቱን እና ሥራውን በአግባቡ ሊያከናውን የሚችል የፍርድ ቤት ማሕበረሰብ መገንባት አስፈላጊ መሆኑን በፍርድ ቤቱ የክቡር ፕሬዚደንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቦጃ ታደሰ ገለጹ፡፡
ለፍርድ ቤቱ የአስተዳደር ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎችና ቡድን መሪዎች በሥነምግባር፣ በሙስና እንዲሁም ተያያዥ በሆኑ ርዕሰ-ጉዳዮች ላይ የተዘጋጀ የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሚያዚያ 26 ቀን 2015 ዓ.ም በፍርድ ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ ተሰጥቷል፡፡

“ሙስናና ብልሹ አሠራርን መከላከልና መልካም ሥነምግባርን...

4296
ለፍርድ ቤቱ አዲስ ሠራተኞች የሙያ ትውውቅ ኮርስ (Induction Training) ተሰጠ
--------------------------------------------------------------------------
በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሥነምግባር መከታተያ ክፍል “ሙስናና ብልሹ አሠራርን መከላከልና መልካም ሥነምግባርን ማስፈን” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሥልጠና ከፍርድ ቤቱ የአስተዳደር ዘርፍ ለተውጣጡ 120 ሠራተኞች ሚያዚያ 21 ቀን 2015 ዓ.ም በፍርድ ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ ተሰጠ፡፡

የአውሮፓ ሕብረት ለፍርድ ቤቱ በሰጠው የገንዘብ ድጋፍ...

3202
በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት በፌደራል ፍርድ ቤቶች ተግባራዊ እንዲሆኑ ለተለዩ የወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ሥራዎች ማስፈጸሚያ የአውሮፓ ሕብረት የመደበው የገንዘብ ድጋፍ ውጤታማ በሆነ መንገድ ጥቅም ላይ እንዲውል የፍርድ ቤቱ አመራሮችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ተገቢውን ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ም/ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ አበባ እምቢአለ ገለጹ፡፡

አጣሪ ጉባዔው በአራት ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

2664
የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሐሙስ መጋቢት 28 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው መደበኛ ስብሰባ በአራት ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ሶስት ጉዳዮች ላይ ለውሳኔ አሰጣጥ እንዲያመች ተጠሪዎች መልስ እንዲሰጡበት አቅጣጫ ሲያስቀምጥ በአንድ ጉዳይ ላይ ተጨማሪ መረጃዎች ተጣርተው እንዲቀርቡ ትእዛዝ በማስተላለፍ በይደር አሳልፎታል፡፡
First5556575860626364Last