Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
6109

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 857 download(s)

«May 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
27282930123
45678910
11121314151617
18192021222324
25262728293031
1234567

የፍርድ ቤቱ አዲስ ተሿሚ ፕሬዝዳንቶች እና በቀድሞ...

2704
መጋቢት 27ቀን 2015 ዓ.ም፡- የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አዲስ በተሾሙ ፕሬዝዳንቶች እና በቀድሞ ፕሬዝዳንቶች መካከል የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳነት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምሕረት (ረዳት ፕሮፌሰር) በተገኙበት የስራ ርክክብ ስነስረዓት ተፈጸመ፡፡

ፍርድ ቤቱ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር ያደረገው ስምምነት የፍርድ...

2116
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከኢትዮጵያ ቴሌኮም ጋር የተፈራረመው የመግባቢያ ስምምነት (Memorandum of Understanding) በዳኝነት አገልግሎት አሠጣጥ ዘርፍ የተሰማሩ የፍርድ ቤቱን ዳኞችና ሌሎች ባለሙያዎች ጫና ለመቀነስና የፍ/ቤቱን አገልግሎት ለተጠቃሚዎች ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ገለጹ፡፡

የፍርድ ቤት ተገልጋዮችን እንግልት የሚቀንሱ እና የፍትሕ...

2393
የፍርድ ቤት ተገልጋዮችን ጊዜ፣ ጉልበት እና የገንዘብ ወጪ የሚቀንሱ እና የፍትሕ እርካታ የሚጨምሩ የማሻሻያ ሥራዎች የሚከናወኑ መሆኑን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ገለጹ፡፡

ፍርድ ቤቱ እና የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት...

2530
የፈደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንሰቲትዩት በቴክኖሎጂ ዘርፍ አብሮ ለመስራት የሚያስችልላቸውን የመግባቢያ ስምምነት በፍርድ ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ መጋቢት 14 ቀን 2015 ዓ.ም ተፈራረሙ።
First5657585961636465Last