Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
7937

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 1013 download(s)

«August 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
31123456

በፌደራል ፍርድ ቤቶች የለውጥ ፍኖተ-ካርታ ላይ ውይይት ተካሔደ

3703

በፌደራል ፍርድ ቤቶች የለውጥ ፍኖተ ካርታ ላይ በጥብቅና ሙያ ተሰማርተው አገልግሎት በመስጠት ላይ ለሚገኙ ጠበቆች በፌደራል ፍርድ ቤቶች ከፍተኛ አመራሮች ሰኔ 17 ቀን 2015 ዓ.ም ገለጻ ተደርጓል፡፡

ለፌደራል ፍ/ቤቶች ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት የተገነባው...

3813

ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት በከፍተኛ ፍርድ ቤት ቅጥር ግቢ አዲስ የተገነባው ባለሶስት ወለል (G+2) ሕንጻ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም በፍርድ ቤቱ ፕሬዚደንት በክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በይፋ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡

ተወላጅነትን በማረጋገጥ እና በመካድ ክርክር እንዲሁም...

4287

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሕጻናት ፍትሕ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ተወላጅነትን በማረጋገጥ እና በመካድ ክርክር እንዲሁም በዘረመል ምርመራ አጠቃቀም ላይ ለፌደራል ፍርድ ቤት ዳኞች ያዘጋጀው የሥልጠና እና የውይይት መድረክ ከሰኔ 10-11 ቀን 2015 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ ተካሒዷል፡፡

በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ንፋስ ስልክ ላፍቶ ምድብ...

3507

በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ስር የተደራጀው የሕጻናት ፍትሕ ፕሮጀክት ከሕጻናት አድን ድርጅት (Save the Children) በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ንፋስ ስልክ ላፍቶ ምድብ ችሎት ያደራጀው የሕጻናት ማስመስከሪያ ማዕከል ሰኔ 8 ቀን 2015 ዓ.ም ተመርቆ ተከፈተ፡፡

First5657585961636465Last