Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ተስፋዬ ደገፋ እና ዶ/ር ትዕዛዙ ተፈራ ፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ጽ/ቤት፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት የሰ/መ/ቁ 259947

ለዚህ የሰበር ክርክር ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን በከፍተኛዉ ፍርድ ቤት አመልካች ከሳሽ፣ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሾች በመሆን መከራከራቸዉን የሥር ፍ/ቤቶች ዉሳኔ ያመለክታል፡፡ ክርክሩ በማህበር በመደራጀት ከተገኘዉ ይዞታ ጋር የተያያዘ ሲሆን አመልካች በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተጠሪዎች ላይ ባቀረቡት  ክስ በ03/08/1990 ዓ/ም ተመዝግቦ በፀደቀዉ የመተዳደሪያ ደንብ መሠረት የተደራጀ ታቦር የመኖሪያ ቤቶች ኅብረት ሥራ ማኅበር አባል በመሆን ተደራጅተዉ ማኅበሩ በሕጋዊ መንገድ ከመንግሥት ካገኘዉ ጠቅላላ ይዞታ ላይ መጠኑ 203.67 ካሬ ሜትር የሆነዉን የክርክሩን ይዞታ   በድርሻ እንደሰጣቸዉና የዚሁ ይዞታ ሕጋዊ ባለመብት ስለመሆናቸዉም በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በመ/ቁጥር 281839 በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ኅብረት ሥራ ጽ/ቤትና በኮልፌ  ቀራኒዮ ክለ ከተማ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት ላይ ክስ አቅርበዉ መብታቸዉ ተረጋግጦ ዉሳኔ እንዲያገኝ የሚል ነው፡መልካም ንባብ…

Previous Article ወ/ሮ ሙርሽዳ ሁሴን እና ወ/ሮ አልፊያ ሁሴን (13) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 257243
Next Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Print
4646

Documents to download

  • 259947(.pdf, 828.26 KB) - 611 download(s)

«April 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
303112345
6789101112
13141516171819
20212223242526
27282930123
45678910

በፌደራል ፍርድ ቤቶች የሴቶችን ተሳትፎና እኩልነት...

1990

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት በፌደራል ፍርድ ቤቶች የሴቶችን ተሳትፎና እኩልነት ለማረጋገጥ የሚረዱ የተለያዩ የፖሊሲ እርምጃዎችን እየወሰደ እንደሚገኝ የፍ/ቤቱ ም/ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ አበባ እምቢአለ ገለጹ፡፡

የፍርድ ቤቱ ዳኞች የሰበር ሂደት በሚመራበት ረቂቅ...

2109

የሰበር የዳኝነት አሰጣጥ ስርዓት ግልጽ፣ ቀልጣፋ፣ ተገማች እና ውጤታማ ለማድረግ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተዘጋጀ ረቂቅ የሰበር የሥነሥርዓት መመሪያ ረቂቅ ላይ ግብአት ለማሰባሰብ የፍርድ ቤቱ ዳኞች ውይይት አካሔዱ፡፡

የወንጀል ህጉ ለህጻናት ትኩረት አለመስጠቱ ከህጻናት ጋር...

2241

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር የተቋቋመዉ የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ጽ/ቤት የካቲት 17 ቀን 2015 ዓ.ም በሕጻናት ጉዳይ ላይ ለሚሰሩ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት፣ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት፣ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ዳኞችና ለሶሻል ወርክ ባለሙያዎች ባዘጋጀዉ የሥልጠና መድረክ ላይ ከህጻናት ጋር ተያያዥነት ላላቸዉ ወንጀሎች መበራከት ዋነኛ መንስኤዉ የወንጀል ህጉ ለህጻናት ትኩረት አለመስጠቱ መሆኑ ተገለጸ፡፡

First5758596062646566Last