Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ እና ኤም.ኢ.ኤስ.ፒ. አፍሪካ ኃ.የተ.የግ. ማህበር ፤የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት የሠ/መ/ቁጥር 251398

የክሱ ይዘት በአጭሩ፡- ከቻይና ሀገር ለሚያስመጣቸው ብራንዳቸው ችንት የዋጋ ግምታቸው ብር 4,899,067.12 (አራት ሚልዮን ስምንት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺህ ስልሳ ሰባት ከ12/100) የሆኑ1,176(አንድ ሺህ አንድ መቶ ሰባ ስድስት) ካርቶን የተለያዩ የኤሌክትሮኒክ ዕቃዎች ከቻይና ተጓጉዘው ሞጆ ደረቅ ወደብ እስኪደርሱ ድረስ ጉድለትን ጭምሮ ለሚደረስ ማንኛውም ጉዳት በመድን ፖሊስ ቁጥር GU/34/2011/2019/00114 አጠቃላይ የመድህን ሽፋን የሰጣቸው ዕቃዎች ሞጆ ደረቅ ወደብ ደርሰው ከሳሽ ከመረከቡ በፊት ዕቃዎች ገበያ ላይ በመታየታቸው ፍተሻ ተደርጎ የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት እንዲፈፀም ህዳር 15 ቀን 2012 ዓ.ም ከሳሽ አቤቱታ አቅርቦ የጉምሩክ ጽ/ቤት ተወካይ፤አጓዡ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት እና የከሳሽ ማኅበር ተወካዮች በተገኙበት ህዳር 17 ቀን 2012 ዓ.ም ዕቃዎቹ የመጡበት ኮንቴነር ተከፍቶ ሲፈተሸ የዋጋ ግምታቸው ብር 1,827,753.64 (አንድ ሚልዮን ስምንት መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ሶስት ከ64/100) የሆነ 171 እሽግ መጉደሉ ተረጋግጦ አጓዡ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት የጎደሉ ዕቃዎችን በዝርዝር በመያዝ ወደ መጋዘኑ ማስገባቱንና ተከሳሹ ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ አጓዡ ኃላፊነት ወስዶ የጉድለት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ስላልሰጠው የካሳ ክፍያ ጥያቄውን ማስተናገድ አልችልም ማለቱን ጠቅሶ ተከሳሹ ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ በገባው የማሪን ውል መሰረት የጎደሉ ዕቃዎች ዋጋ 1,827,753.64 (አንድ ሚልዮን ስምንት መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ሶስት ከ64/100) ካሳ ማስጠንቀቂያ ከደረሰው ከግንቦት 28 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ከሚታሰብ ሕጋዊ ወለድ፤ ከወጪ እና ኪሳራ ጭምር እንዲከፍለው ጠይቋል፡፡መልካም ንባብ….

Previous Article ሲሲኢሲሲ ኢትዮጵያ ቅርንጫፍ እና አቶ ቤልሻጽር ሀይለልዑል መ/ጽድቅ የሰ.መ.ቁ.250942
Next Article የፌደራል ዐቃቤ ህግ እና አቶ አበበ ወንድሙ ኤጋ የሰ/መ/ቁጥር 251759
Print
1822
«November 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
1234567

ባለፉት ሶስት ዓመታት በተከናወኑ የማሻሻያ ስራዎች ተስፋ...

1714

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ በፌዴራል ፍርድ ቤቶች እየተከናወኑ ባሉ የማሻሻያ ስራዎች ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መገኘታቸውን የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ዳኞችና የአስተዳደር ዘርፍ ሃላፊዎች እንዲሁም የስር ፍርድ ቤቶች ፕዝደንቶችና ም/ፕሬዝደንቶች በተገኙበት በተካሄደ የውይይት መድረክ ላይ ገለጹ፡፡

የውይይት መድረኩ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ከጀስቲስ ፎር ኦል- ፐሪዝን ፌሎው ሺፕ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ ሂደት የፍርድ ቤቶች ሚናን አስመልክቶ ዳኞች በሙያቸው ያገኙትን ዕውቀትና እና አመለካከት እርስ በእርስ እንዲለዋወጡ ማስቻል እና የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የማሻሻያ ስራዎች ያስገኙትን ውጤት መገምገም ዓላማ ያደረገ ነው፡፡

ፍርድ ቤቱ በስትራቴጂያዊ እና ዓመታዊ ዕቅዱ ላይ ለምክር...

1734

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ ፍትህና የዲሞክራሲ ጉዳዩች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበው ጥያቄ መሰረት ፍርድ ቤቱ ባዘጋጀው ሶስተኛው ስትራቴጂያዊ ዕቅድ እና ዓመታዊ ዕቅድ ላይ ማብራሪያ ሰጠ፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ በፍርድ ቤቱ በኩል ዕቅዶቹን አስመልክቶ ሰፊ ማብራሪያ ከመቅረቡ በፊት በሰጡት አጭር ገለጻ የዳኝነት ዘርፉ በአማካሪ ድርጅት በመታገዝ ስትራቴጂያዊ ዕቅዱን ማዘጋጀቱን፤ የዕቅዱን ይዘትና አዘገጃጀት ሂደት የሚከታተል በየደረጃ ያሉ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አመራሮች፣ የስራ ክፍል ኃላፊዎችና ባለሙያዎች አባል የሆኑባቸው ዓቢይና ቴክኒክ ኮሚቴ መቋቋማቸውን፤ በረቂቅ ዕቅዱ ላይ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ማህበረሰብ እና ባለድርሻ አካላት መወያየታቸውን እና የተገኙ ተጨማሪ ግብዓቶችን በማካተት ተዘጋጅቶ የጸደቀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የሙስና ወንጀልን በትብብርና በአንድነት መንፈስ መከላከል...

1617

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የፕሬዚደንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቦጃ ታደሰ የሙስና ወንጀልን በትብብርና በአንድነት መንፈስ መከላከል እንደሚገባ ገለጹ፡፡

አቶ ቦጃ ታደሰ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በዓል አከባበርን አስመልክቶ በተዘጋጀ የገንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መድረክ ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ሙስና ሕዝብ በመንግሥት እና በሕግ የበላይነት ላይ አመኔታ እንዲያጣ የማድረግ ጉልበት ያለው መሆኑን በመጥቀስ፣ ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ልማትን በእጅጉ በማዳከምና በመጉዳት የሞራልና የሥነምግባር ቀውስ እንዲፈጠር የሚያደርገውን የሙስና ወንጀል በትብብርና በአንድነት መንፈስ መከላከል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የሴቶችና...

1251

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሴቶችና ሕጻናት ዙሪያ የሚኖርን የፍትሕ ተገማችነትን ለማስፋት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ሥርዓተ-ችሎት እንዲዘጋጅ እያደረገ እንደሚገኝ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ም/ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ አስታወቁ፡፡

ም/ፕሬዚደንቱ ይህን ያስታወቁት የፌደራል ፍ/ቤቶች ዓለም ዓቀፍ ፀረ-ጾታዊ ጥቃት ቀንን ሕዳር 30 ቀን 2014 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት አዳራሽ በፓናል ውይይት ሲከበር ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ነው፡፡

First5859606163656667Last