Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ኃይለ ጊዮርግስ ይልማ ወልደአብ እና እነ አቶ አዲስ እሸቱ (4) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 252056

ለዚህ የሰበር አቤቱታ ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን በወረዳዉ ፍርድ ቤት 1ኛ ተጠሪ ከሳሽ የአመልካች አዉራሽ ሟች አቶ ይልማ ወልደአብና ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ 1ኛ ተጠሪ በጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተራ ቁጥር ላይ በተጠቀሱት ተጠሪዎችና በአመልካች አባት በሟች አቶ ይልማ ወልደአብ ላይ ባቀረቡት ክስ በክሱ ላይ አዋሳኞቹ የተመለከተዉን 400 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈዉን  የመኖሪያ ቤት ከነሰርቪስ  ቤቶቹ ጭምር የካቲት 27 ቀን 2011 ዓ/ም በተፈረመ የሽያጭ ዉል ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (ከሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) በብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ) ገዝተዉ ካርታ በስማቸዉ የተሰጣቸዉ ቢሆንም በይዞታዉ ላይ ካሉ ቤቶች መካከል አንዱን የአመልካች ወላጅ አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) ይዘዉ ለመልቀቅ ፈቃደኛ አለመሆናቸዉን ገልፀዉ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (የሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) የሸጡላቸዉን ቤት ከአመልካች አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) አስለቅቀዉ እንዲያስረክቡና የአመልካች አባትም (የሥር 4ኛ ተከሳሽም) መብት ሳይኖራቸዉ የያዙትን የ1ኛ ተጠሪን (የሥር ከሳሽን) ቤት ለቀዉ እንዲወጡ እንዲወሰንላቸዉ ዳኝነት በመጠየቅ ክስ አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ….

Previous Article የፌደራል ዐቃቤ ህግ እና አቶ አበበ ወንድሙ ኤጋ የሰ/መ/ቁጥር 251759
Next Article የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አቶ መጣልኝ መላኩ የሰ.መ.ቁ.252953
Print
6052

Documents to download

  • 252056(.pdf, 838.15 KB) - 680 download(s)

«August 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
31123456

ፍ/ቤቶች የሕጻናትን መብቶችና ጥቅሞች ከማስከበር አንጻር...

3920

የፌደራል ፍ/ቤቶች የሕጻናትን መብቶችና ጥቅሞች ከማስከበር አንጻር ያለባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት የተለያዩ ጥረቶችን በማድረግ ላይ እንደሚገኙ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ ሌሊሴ ደሳለኝ ገለጹ፡፡

በመቀሌ ስካሄድ የነበረዉ የፌደራል እና የክልል ፍርድ...

3867
(ግንቦት 19/2015 ዓ.ም) በአዉሮፓ ህብረት ቴክኒካዊ ድጋፍ በኢትዮጵያ የወንጀል ፍትህ አስተዳደር ሪፎርም የሚደግፍ ፕሮጀክት ተቀርጾ እየተከናወነ የመሚገኘኝ ሲሆን ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ የኢትዮጵያ መንግስት የወንጀል ፍትህ አስተዳደር ሪፎርም ሥራዎች የሚደግፍና የፌደራል ፍርድ ቤቶች እና የክልል ፍርድ ቤቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነዉ።

በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የዘጠኝ ወር ዕቅድ አፈጻጸም ላይ...

3838
በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ዘርፍ የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የዘጠኝ ወር ዕቅድ አፈጻጸም ላይ የተዘጋጀ ውይይት በፍ/ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ ግንቦት 12 ቀን 2015 ዓ.ም ተካሔደ፡፡

የሕጻናት ፍትሕ ፕሮጀክት ጽ/ቤት በሕጻናት የቅብብሎሽ...

7073
በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የሕጻናት ፍትሕ ፕሮጀክት ጽ/ቤት በፍትሕ ሥርዓቱ ውስጥ የሚያልፉ ሕጻናት የዘርፈ-ብዙ አገልግሎት ተጠቃሚ በሚሆኑበት የቅብብሎሽ ሥርዓት ዙሪያ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ ግንቦት 8 ቀን 2015 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ ጎልድ ማርክ ሆቴል ተካሂዷል፡፡
First5859606163656667Last