Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
6109

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 857 download(s)

«May 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
27282930123
45678910
11121314151617
18192021222324
25262728293031
1234567

በፌደራል ፍርድ ቤቶች የሴቶችን ተሳትፎና እኩልነት...

2112

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት በፌደራል ፍርድ ቤቶች የሴቶችን ተሳትፎና እኩልነት ለማረጋገጥ የሚረዱ የተለያዩ የፖሊሲ እርምጃዎችን እየወሰደ እንደሚገኝ የፍ/ቤቱ ም/ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ አበባ እምቢአለ ገለጹ፡፡

የፍርድ ቤቱ ዳኞች የሰበር ሂደት በሚመራበት ረቂቅ...

2252

የሰበር የዳኝነት አሰጣጥ ስርዓት ግልጽ፣ ቀልጣፋ፣ ተገማች እና ውጤታማ ለማድረግ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተዘጋጀ ረቂቅ የሰበር የሥነሥርዓት መመሪያ ረቂቅ ላይ ግብአት ለማሰባሰብ የፍርድ ቤቱ ዳኞች ውይይት አካሔዱ፡፡

የወንጀል ህጉ ለህጻናት ትኩረት አለመስጠቱ ከህጻናት ጋር...

2368

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር የተቋቋመዉ የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ጽ/ቤት የካቲት 17 ቀን 2015 ዓ.ም በሕጻናት ጉዳይ ላይ ለሚሰሩ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት፣ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት፣ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ዳኞችና ለሶሻል ወርክ ባለሙያዎች ባዘጋጀዉ የሥልጠና መድረክ ላይ ከህጻናት ጋር ተያያዥነት ላላቸዉ ወንጀሎች መበራከት ዋነኛ መንስኤዉ የወንጀል ህጉ ለህጻናት ትኩረት አለመስጠቱ መሆኑ ተገለጸ፡፡

First5859606163656667Last