Selam Warga / Tuesday, June 17, 2025 / Categories: CASSATION, Cassation አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395 ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594 Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230 Print 8048 Documents to download 266395(.pdf, 849.74 KB) - 1020 download(s)
ፍ/ቤቶች የሕጻናትን መብቶችና ጥቅሞች ከማስከበር አንጻር... ፍ/ቤቶች የሕጻናትን መብቶችና ጥቅሞች ከማስከበር አንጻር... Monday, June 5, 2023 3914 የፌደራል ፍ/ቤቶች የሕጻናትን መብቶችና ጥቅሞች ከማስከበር አንጻር ያለባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት የተለያዩ ጥረቶችን በማድረግ ላይ እንደሚገኙ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ ሌሊሴ ደሳለኝ ገለጹ፡፡ Read more
በመቀሌ ስካሄድ የነበረዉ የፌደራል እና የክልል ፍርድ... በመቀሌ ስካሄድ የነበረዉ የፌደራል እና የክልል ፍርድ... Monday, May 29, 2023 3850 (ግንቦት 19/2015 ዓ.ም) በአዉሮፓ ህብረት ቴክኒካዊ ድጋፍ በኢትዮጵያ የወንጀል ፍትህ አስተዳደር ሪፎርም የሚደግፍ ፕሮጀክት ተቀርጾ እየተከናወነ የመሚገኘኝ ሲሆን ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ የኢትዮጵያ መንግስት የወንጀል ፍትህ አስተዳደር ሪፎርም ሥራዎች የሚደግፍና የፌደራል ፍርድ ቤቶች እና የክልል ፍርድ ቤቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነዉ። Read more
በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የዘጠኝ ወር ዕቅድ አፈጻጸም ላይ... በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የዘጠኝ ወር ዕቅድ አፈጻጸም ላይ... Monday, May 22, 2023 3821 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ዘርፍ የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የዘጠኝ ወር ዕቅድ አፈጻጸም ላይ የተዘጋጀ ውይይት በፍ/ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ ግንቦት 12 ቀን 2015 ዓ.ም ተካሔደ፡፡ Read more
የሕጻናት ፍትሕ ፕሮጀክት ጽ/ቤት በሕጻናት የቅብብሎሽ... የሕጻናት ፍትሕ ፕሮጀክት ጽ/ቤት በሕጻናት የቅብብሎሽ... Wednesday, May 17, 2023 7053 በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የሕጻናት ፍትሕ ፕሮጀክት ጽ/ቤት በፍትሕ ሥርዓቱ ውስጥ የሚያልፉ ሕጻናት የዘርፈ-ብዙ አገልግሎት ተጠቃሚ በሚሆኑበት የቅብብሎሽ ሥርዓት ዙሪያ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ ግንቦት 8 ቀን 2015 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ ጎልድ ማርክ ሆቴል ተካሂዷል፡፡ Read more